Sunday, January 30, 2011

መሪሕ ውድብ የተባለ ፖለቲካዊ ታቦት እያለ የዓረቦች አደባባይ አብዩት ባሁኗ ኢትዩጵያ አይሰራም

ይድረስ ለጎጠኛው መምህር (አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ ( ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com

ብዙዎቹ-የተቃዋሚ ድረገጾች፤ የተማሩ የፖለቲካ ተንታኞች-ኢትዮጵያውያንና የተገንጣይ ቡዱኖች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ ዓረብ ዓለም ውስጥ ካለው ሁኔታ እና ሕሊና አንድ አድርገው ሲመለከቷቸው ሰሞኑን ታዝቤአለሁ። በግብፅ በቱኒዝያ እና በየመን በኢራን በፓኪስታን በኢራቅ በመሳሰሉት የዓረብ እና የእስላም አገሮቸ ያለው የመንግሥት ጭቆና ከማንም ዓለም ጋር ካገራችንም ጭምር የሚያመሳሰሉበት ሁነታዎች ቢኖሩትም አብዛኛዎቹ ምሀራን ሲገመግሙ ወይንም ሲያመሳስሉ የጭቆናው መልክ ተመሳሳይነት በመመርኮዝ ብቻ ባገራችንም የቱኒዝያ ወይንም የየመን እና የግበጾች ዓይነት ያደባባይ በዓመጽ የታጀበ ሕዝባዊ የሥርዓት ተቃውሞ በቅርቡ እንደሚከሰት ተንብየዋል። ያ ግን ኢትዩጵያ ምድር ውስጥ አይሰራም። ለምን?

ምክንያቶቹ ብዙ ናቸው። የአረቦቹ/የእስላም አገሮች የመሰለ ሕዝባዊ የጎርፍ ዓመጽ የማይከሰትብት ቀንደኛው እንቅፋት አንዱ “አገራዊ ፍቅር አነግቦ ከእሳት ጋር የሚጋፈጥ የኢሕአፓ ዓይነት ወጣት” ኢትዮጵያ ውስጥ የለም! ለወደፊቱም አይበቅልም። ያ ወጣት ከነ ብዙ ግብታዊ ስሕተተቶቹ በምንም መልኩ የሚወዳደረው ያ ትውልድ መሳይ ጠንካራ ልበ ደንዳና ወጣት በዓፍሪካ ቀርቶ በዓለምም አይኖርም”። ስለሆነም ሕዝቡ ያ ዓይነት ወጣት በሕጋዊነት /በይፋ የሚንቀሳቀስ በብዛት ስለሌለው ክፍተቱ ሕዝቡ ለጥቃት ተጋልጦ ረግቶ ተቀምጧል። ያ ክስተት እንዳለ ሆኖ፦“የአሁኑ የዜጎች ሕሊና ከቀደምቷ ኢትዮጵያ የሕሊና አስተሳሰብ በእጅጉ የተለየ ነው”። ግበጾች፤የመኖች፤ቱኒዝያዎች አገራችን የሚሏት ዬራሳቸው አገር እንዳላቸው ያምናሉ፡ በዛሬቱ ኢትዮጵያ ያለው ዜጋ ግን አርባ ኣራት ባነዴራ ለብሶ እአውለበለበ አገሬ የሚላት አገር በሕሊናው የተቀረጸች አገር የለውም። የተምታታ ሕሊና ፤የተምታታ አገራዊ ስሜት ያነገበ ነው። አገሩ ለሱ አውራጃው እና ብሔሩ እንዲሆን ላስራ-ስምንት ዓመት ተሰብኳል፡፤ መሸጥ መንከባከብ መለወጥ ማስተላለፍ መስጠት የሚያሽችል የመሬት ባለቤትነት እትብት የሌለው ገበሬ እና የከተማ ኗሪ የዜግንት ምንነት እትብቱ በጠመንጃ ሃይልና በብሔረተኛ ክልልተኛነት ስሜት የተበጠሰበት ዜጋ ስላለቺው “አገር” ደንታ እንዳይኖረው አድርጎታል። ደንታውና አትኩሮቱ “ከራሴ በፊት ላገሬ ለሰነደቃላማዬ” ሲባል የነበረው የጥንት መርሆ ሳይሆን ከለት ዕለት ከመራሹ መነግሥት ተከራይቶ የሚያገኛት የምግብ ማስጌኛ ብጣሽ እርሻ መሬቱ ራሱን እንዴት ማስኖር እንደሚችል የታጠረ ሕሊና ውስጥ የገባ ማሕበረስብ ነው። ሕዝባዊ ዓብዮት የሚቀሰቀስ አገሬ የሚላት አገር ስትኖር ነው። ዛሬ አገሬ የሚላት አገር የሌለው የተምታታ ሕሊና “መንግሥት ለውጦ” ስለ አገር የሚቆረቆር ሕሊና የሚዋደቅ ሃገራዊ ፓን ኢትዮጵያኒዝም ማሕበረስብ የለም።ከኖረም ጥቂት ነው። ቆሞ በድፍረት ኢትዮጵያ ትቅደም ብሎ በጠባብ ብሔረተኛው ሥርዓት ፊት ዓብዮት የሚያስነሳ ሕብረተሰቡን በግምባር ቀደም መምራት የሚችል ወጣት ተቃዋሚ ስለሌለ ሕብረተሰቡ የማይንቀሳቀስ የረጋ ውሃ አድረጎታል።

ለሕብረተሰብ ግበታዊም ሆነ አዝጋሚ ለውጥ ለማምጣት ያገሩቱ ወጣት ራሱን በኢትኦጵያዊነትና በዓለም አቀፋዊ የሕዝቦች አንደነት የሚያምን ወጣት ሲገነባ ወይንም ሲኖራት ዓብዮት/ዓመጽ ሊከሰት ይችለላል። በኢትዮጵያ ሁኔታ ዛሬ ያለው ወጣት “ኢትዮጵያዊ” ወጣት ሳይሆን “ትበገራዊ”፤ “ኦሮሚያዊ” “ወላይታዊ’ ሶማሊዊ፤ በአደሬዊ…..ነት የተጠለፈ ወጣት ነው። የተለያዩ ነገዶች የምታስተናግደው በአገሪቱ ርዕሰ ከታማ የምትገኘው የቀዳማዊ ሃይለስላሴ/አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስንመለከት ተማሪው በትግራዊነትና በኦሮሚያዊነት አጥር አጥሮ ቅራኔ ፈጥሮ ሲካሰስ፤ ሲጋደል እና ሲናቆር የሚገኝ ወጣት ነው። በገጠሩ ማሕበረሰብ በኦሮሞ ገጠሮች ውስጥ ተሰማርቶ ሕጻናት ልጆቹን ጭሮ ግሮ የዕለት ምግቡ ለመመገብ የሚፍጨረጨር የአማራ አዛውንት፤ወጣት እና አመጫት በአማራነቱ እየታፈሰ እየተገደለ እመቻት ከሕጻናት ልጆቻቸው ወደ እሳት እየተጣሉ ሕይታቸው ለማትረፍ ሲሸሹ እንደ ጀግራ በጥይት ሲታደኑ ወጣቱ በየትምሕርተ ተቋዋማቱ እሱም በአማራነትነ በኦሮሚያዊነት ወይንም በትግራዊነት ዜግነት እና ማንንት ገብቶ የሚዳክር እና ወደ ገዢው ቡድን ሳይሆን ወደ ራሱ እርስ በርሱ በድንጋይ የሚወራወር እና በቢላዋ የሚጨፋጨፍ ወጣት ስላልነቃው ሕብረተሰብ ደህንነት እና እጣ ፈንታ ስለ መንግሥት አስተዳዳር ለውጥ ደንታ የሌለው አድርጎታል።

በመቶዎች የሚቆጠሩ ወያኔ ሰራሽ ባንዴራዎች ተሸፍኖ ኦሮሚያ ዊ ትገራዊ አደሬዊ፤ሶማሊዊ፤ጉራጌዊ፤ሃዲያዊ፤ከምባታዊ የደቡብ ሕዝቦች ብሔር ብሔረሰብና ሕዘቦች ዊ…. የማንነት ተኮር መታወቂያ እንዲይዝ ሲታዘዝ ተቃዉሞ የላሰማ ወጣት እንዴት ሲኮን አገር አለን ብለው ከሚታገሉ አንድ ሰንደቃላማ እያውለበለቡ ሁሉም አንዲቷን ሰንደቃላመቸውን እየሳሙ እና ለብሰዋትና አንድነት ከበሬታ ኪመጮኹ የግብፆች፤ቱኒዚያዎች፤ የመኖች፤ ኢራን… ወጣቶች ጋር ትይዩ አድርጎ በኢትዮጵያም ተመሳሳይ ዓብዮት ሊከሰት ነው ማለት እንችላለን?

ስለ ተቃዋሚ መሪዎች ማንሳት በሽታ ስለሚቀሰቅስ ሳይነሳ ብንተወውና በዛው በማይረባው ተቃዋሚ ባንነጋገርም ቱኒዚያዎች እና ግብጾች ያለ መሪ ነበር ተነስተው ውጤት እንዲከሰት ያደረጉና እኛም ጋር ሊከሰት ነው፤ ብለው ተንታኞቻችን ተብየዎች ቢተነበዩም፤ የነዚህ አገር ወጣት እና ሕዝብ ከኛው ጋር አይመሳሰልም፤፡ ከላይ ያስቀመጥቁት ምክንያት እንዳለ ሆኖ -የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የ እስላም /ዓረብ አገሮች ሕዝቦች ህሊና እጅግ የተለያዩ ተጻራሪዎች ናቸው። የእነዚያ “ድፈርት” ሞት መጋፈጥ ጽድቅ ነው ይላሉ። “አላህ ወ አክበር!!!!” በማለት የጋራ መፈክር አነግበው የሚነሱ ዓመጽ ሲያስነሱ ወደ ስካርነት የሚያዘነብል ቆራጥ ሕሊና አላቸው። “አላህ ወ አክበር” የሚለው የጋራ መፈክር ሕሊናቸው የሚያስነሳ ፓርቲ/ደርጅትን ተመስሎ የን ያከል በአንድነት ስሜት ስለሚያስተሳስራቸው የሚጋፈጡት ጠላትና ስርዓት በቆራጥነት ይገፈጡታል። መንፈሳዊ የጋራ መፈክራቸው ከፖለቲካ ተቃዋሚ ድርጅት መሪ በላቀ መልኩ “በጋራ ወደፊት እንዲስፈነጠሩ ሃይለኛ መጎድ የሚፈጥር ሃይማኖታዊ የሕሊና ትጥቅ አላቸው። በግብጻች የታየውና የሚታየው በክርስትያኑ እና በሕዝብላህ (ኢስላሚክ ብራዘር ሁድ) ያለው ቅራኔ እስከመገዳደል የደረሰ ቢሆንም ቅራኔው ሃይማኖታዊ እንጂ እንደ አገራችን ፖለቲካዊ ስላልሆነ በጋራ ቆመው ስርዓቱን ይቃወማሉ። ያገራቸን ከዚህ ሁሉ የተለየ ነው።

ኢትዮጵያዊ ሕሊና ግበረገቡ ያስተማረው “ትሕትና፤አክብሮት፤ዝግታ፤ትዕግሥት፤ረጋ ማለት፤መንግሥትን፤ዓዋጅን እና ሕግን ማክበር…” ነው። ካሪዝማቲክ (ትግሬዎች ጦብላሕታ- የምንለው “ሸጋ ባሕሪ”) የሚሉት ዓይነት። ቫዮለንት/ሞገደኛነትን ይኮንነናል። ያ ባሕል እና ተፈጥሯዊ ባሕሪ ዛሬ የወያኔ ወመኔ መሪዎች ወደ ራሳቸው መጠቀሚያ በማዞር “ዕድገትና ልማት” “ሰላምና መረጋጋት” የሚላቸው በአሻጥራዊ/አታላይ ውጥመድ መፈክሮች አስገብቶ ሁሉም በነዚህ ወጥመዶች እየተታለለ “በ አልሙናይ፤ እና ባውራጃ፤ በወረዳነት አና በክለልተኛነት” ታጥሮ “መሪሕ ውድብ” (መሪ ድርጅት) ብሎ ለሚጠራው ፖለቲካዊ የሆነ ወደ “ታቦትነት” የተጠጋ “መሪሕ ውድቡ” እንዲከተል በግድም በውድም ሕሊናው ሰግጦ ይዞታል። ይህ መሪሕ ውድብ (መሪ ድርጅት) ኮሚኒስታዊ/ፋሺስታዊ በመሆኑ ሥልጣን ተዋረድ በሰንትራሊዝም/ማዕከላዊነት ስለሚንቀሳቀስ “ በአፓርታይድ ዓይነት የተዋቀሩ ክልሎች” መሪህ ውድቡ (ድርጅቱ ወያኔ/ኢሕአዴግ) የሚያዘውና የሚያስተላልፈው ሁሉ በመፈጸም “በሰላምና መረጋጋት” የማታለያ መፈክር ገብቶ ከአመጽ እንዲርቅ ትምህርት ቤቶች/መጻሕፍተ ቤቶች ብቻ በማነጽ እንዲያተኩር የፖለቲካው ጨዋታ “መሪሕ ውድቡ” ለተባለው የማይገሰስ የማይወቀስ “ፓለቲካዊ ታቦት” ሃላፊነት እና ዕምነት በመስጠት ሕሊናው በህንጻ ግምባታ ተኮር እንዲሆን ስላደረገው ሰማይ ጠቀስ ሕንጻዎች ቆሞ መጽሕፍተ ቤቶች በመጻህፍት ተሞልተው በማየት “ምርቃና” ውስጥ ገብቶ በመሪሕ ውድቡ ላይ እንዳያምጽ የስነ ኣእምሮ ሰላባ በማካሄድ “ሕሊናው ወደ መጎድ” እንዳያዘነብል “ልማትና መረጋጋት” “በመሪሕ ውድቡ” (ብቸኛ የሠርቶ አደር መሪ ድርጅቱ) እየተመራ ጥቂቶች እየተንደላቀቁ ብዙሃኑ በሰላምና መረጋጋት “ዲሲፕሊናዊ መፈክር” አስገብቶ ኢትዮጵያዊ መንግሥት አክባሪነት እና ለሕግ ተገዢነት ባሕሪው ባሰዛኝ ሁኔታ ሰልቦታል።

በቁሙ የተሰለበ ሕሊና ደግሞ አመጽ ላመስነሳት እጅግ አዝጋሚ ከመሆኑ የተነሳ አሁን ካለው የተለየ አስተሳሰብ ያለው ፓን ኢትዮጵያኒዝም ያነገበ ወጣት በታምር ካልተፈጠረ “መሪሕ ውድብ” የተባለ “ፖለቲካዊ የፋሽስቶች/ኮሚኒስቶች ታቦት” እያለ የዓረቦች ዓብዮት በኢትዮጵያ ውስጥ ሊከሰት አይችልም። የሚከሰት ከሆነ ባለፈው ጊዜ ካስቀመጥኳቸው ሦስት ዓይነት ሚሊታሪ/ወታደራዊ/ኩዴታዎች/መፈንቅለ መንግሥት ሊከሰት ይችል ይሆናል (ያ ደግሞ አሁን ሊሆን አይችልም)፡ ያ ሲሆን ደግሞ “መረሪሕ ውደብ” ተብሎ ሥልጣን ላይ ያለው “ፖለቲካዊ ታቦት” ሲደፈር ጠባብ ብሄረተኛውና ጽንፈኛው የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ አመራር አባል ስብሓት ነጋ “መንደር መንደራችን” አንድንይዝ በፌርማው አጽድቆልን እሱም ወደ መንደሩ ወደ “ዓዲ ኣቡን” (ዓድዋ) ኦነግ እና ኦጋዴኒያንም ወደ ገጠሪቱ ኦሮሚያ ሪፑብሊክ እና ወደ አጋዲኒያ ምድረበዳ መንደር መንደራቸው ይዘቀው እንሱም በታራቸው ሕዘቡን ልቀትቅጥህ ብለው ህዝቡን ማስለቀስና እርስ በርስ በመንደር የሥልጣን ሽኩቻ ይቀጣቀጣሉ።

ያፍሪካ ቀንድ ተብሎ የሚጠራው ኤርትራም ውስጥ “ያሉት 9 ብሔር ብሔረሶቦች” ደግሞ ኩናማው ዓፋሩ ሳሆው ናራው ብሌኑ ትግራዩ ትግራይ ትግሪኙ የእሳቱ ጭድ በመሆን እርስ በርስ መግባባት አቅቶት “በባቢሎን ግምብ ገምቢዎች ቋንቋ” መነጋገር ይጀምራል ማለት ነው። ያ ሲሆን እንገንጠል ሲሉ የነበሩት የዲአስፖራ የግንጠላ አቀንቃኞች ልጆቻቸው በሰላም እና መረጋጋት አሜሪካ እና ኢወሮጳ በ ፒ ኤች ዲ አስመርቀዋልና “ወይ ፍንክች የአባ ዋራ ልጅ!” ከምኔሶታ ወይ ንቅንቅ! “አንድ ኢንች መነቃነቅ የለም !!!!!” አሉ አይደል ጓድ መንግሥቱ ሃይለማርያም! “ሀገረ ኤርትራ” ከተባለች “ነፃነት! ነፃነት መፂኣ! እያለ ከእልልታውና ከከበሮው” በሗላ ከጣሊያን ከአሜሪካ ከለንደን ከ አምስተርዳም ከጀርመን ከአውስተራሊያ ከሳውዲ ከኢትዮጵያ አንድ ኢንች መነቃነቅ የለም!!! ብሎ ኤርትራና! ኤርትራና! ኤሬ! ኤሬ! ብሎ የጮኸ ሁሉ “መሪሕ ውድቡ” አሜሪካና አውሮጳ አድርጎ የለ! ከሳተላይት ቲቪ ከማንደይ “ፉት ቦል” እና “ካሜሪካን አይድል ሾው” ከገነት ርቆ “የልጠተረገችውን ገጠር ኦሮሚያ” እና “ኦጋዴኒክ ሪፓብሊክ” ማን ኩራዝ አብርቶ ሊኖር? ሆ!ሆ! ሞኝህን ፈልግ!

ስለሆነም የዓረቦች የአደባባይ አብዩት የሚከሰት ከሆነ ስብሃት ነጋ እንዳለው “ሁሉም መንደር መንደሩ” እንዲይዝ ከተፈቀደለት በሗላ “ከተሞች ወደ ገጠር እና መንደርነት ሲለወጡ፤ የእርሻ ቦታዎች የወታደራዊ ማሰልጠኛ ሲሆኑ አስቀድሞ በዋሾች እና ባገር በቀል የውጭ ቅጥረኞች የተሰበከው የ “ሚልክ ኤንድ ሃኒ/Milk & Honey” ሰበካ ወደ ማይጨበጥ ሕልም ሲቀየር፤ ቁጭቱ፤ ወደ ምሬት አምርቶ ግጭት ሲጋብዝ ያኔ ‘በዋሾቹና የመንደር ልዑላን እና ነገሥታቶች” ላይ የዓረቦች የአደባባይ አብዩት የሚመስል ዓመጽና ምሬት ሊከሰት ይችላል። የሶማሌ ዓብዮት እንደ ማለት! አርስ በርስ መበላላት ፤መተላለቅ፡ የመቶ ዓመት ሥራ ቤት የመጠናቀቅ ሂደት እንደ ማለት! ማሰሪያው ኢትዮጵያዊ ሕሊና መሪ አክባሪ ነውና ያለ መሪ ራሱ በራሱ አነሳስቶ ለዓመጽ የመነሳት ልምድ እና ባሕል ስለሌለው የረጋ ወተት ሆኖ ለጊዜው መጠበቁ አይቀሬ አሳዛኙ መርዶአችን ነውና ለሃዘን እንቀመጥ! ስለሆነም ነው ብርቱካን መዲቅሳን ቀና ካለችበት ጎራ ተመልሳ እንዳታንሰራራ አደርጎ ከፖለቲካው ውጭ ነኝ በማለት የታምራት ላይኔን ዕጣ ፈንታ ገጥሟት እሷም “ጌታ እሱስ” ፍለጋ ቁልቢ ገብሪኤል መሄዷ አንዱ የአዲሱ ዓብዮት/የታሃድሶ ሕይወት መንገድ ፍለጋ ምልክት በዜና መበሰሩን ከልቦናችሁ በመያዝ፤ “ጌታ እየሱስ” ያበሰራችሁን ዜና ከልቦናችሁ ያሰድረው ያሳድርልን! አሜን! እንበል 12! አመሰግናለሁ። ደህና እንሰንብት! ጌታቸው ረዳ ኢትዩጵያን ሰማይ አዘጋጅ።www.ethiopiansemay.blogspot.commailto:getachre@aol.com%5C

Tuesday, January 25, 2011

The lie has become not just a moral category but a pillar of the state

ይድረስ ለጎጠኛው መምህር (አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ ( ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com\ <አንዱ ሲቋጥር አንዲ ሲፈስበት የተቸገረው የጫካው መንግሥት ጌታቸው ረዳ የዘመናችን መንግሥት “ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ” ይባላል። ይህ ከጫካ የተሰጠን መንግሥት አስራ ስምንት ዓመት ሙሉ ብቻ ሳይሆን ከትግራይ የጫካ መንግሥትነቱ ጀምሮ ቢሰላ አንዱ ሲቋጥር አንዱ ሲፈስበት ከ34 ዓመት በላይ አስቆጥሯል። ይህ ቡድን ሲመሠረት ከተማሪዎች እንቅስቃሴ ዘመኑ የተከተላቸው ፍልስፍናዎቹ ብንመረምር ከግልብ የለውጥ ስሜቱ አንስቶ በወረቀት ያሰፈራቸው ከምስራቁም ከምዕራቡም ቦጫጭቆ በመለገብ ለሕዝባችን ያስለበሰው ቡቱቶ ፍልስፍናው ለዛሬው ኑሮአችን ብቻ ሳይሆን የነገውንም ስጋት ጨምሮብናል። ከጫካ ዘመኑ ጀምሮ ይህ ቡድን የተከተላቸው መንግዶች ከተራ የሽፍቶች ባሕሪ አልፎ በዓለም አቀፍ የተራቀቁ ምስጢራዊ የሽብር አሰራሮች ከተከተሉት የግድያ እና የሽብር እንዲሁም ሕገወጥ የገንዘብ ድለባ ወደ ማካበት የተሸጋገረ በዓይነቱ እጅግ የተለየ አፍሪካዊ ሽብርተኛ የሽምቅ ተዋጊ መንግሥት ለመሆን በቅቷል። ሰሞኑን እየታዘብነው ያለነው የዋጋ ግሽበት በሌሎቹ የኢትዮጵያ ክፍሎች ቀርቶ ብዙ ዋሾ ካድሬዎቹ እና ሚዲያዎቹ በሚኖሩባት ትግራይ ውስጥም ቢሆን ከቅርብ ወራት በፊት አገሪቱ አደገች፤ገበያው ነፃ ገበያ ነው…በማለት ሲዋሹን እና በሕሊናችን ሲዛበቱብን እንዳልነበረው ሁሉ ዛሬ የሪፖርተር ዘጋቢ በትግራይ በተለይም በመቀሌ ከተማ ምግብ ቤቶች እና ሱቆች በሥርዓቱ አገልጋዩች እየታሸጉ እንደሆነ ዘግቦታል። እነኚህ ባለሃብቶች ተቋሞቻቸው የታሸጉበት ምክንያት የዋጋ ንረት ተከትሎ ሸማቹ/ተጠቃሚው ሕብረተስብ ፍጆታዎችን የመግዛት አቅሙ መግዛት ከማይችልበት አቅም በመድረሱ፤ ለዋጋው ንረት ተጠያቂው ነጋዴውን በማድረግ የሚሸጡበትን የዋጋ መጠን በማውጣት፤ትዛዙን የተላለፉ ነጋዴዎች “ትዛዝ ባለማክበር” እየወነጀለ ተቋሞቻቸው እንዲታሸጉ አድርጓል። ይህ ድርጊት ቀደም ብሎ አዲስ አባባ ከተማ ውስጥ እንደታየ እና ውጭ አገር እዚሁ እኛ ጋር የሚኖሩ የሥርዓቱ ተከታዮች ልክ እንደጌቶቻቸው እኛኑን አንደዋሸን በመወንጀል በየዌብሳይቶቻቸውና በፓልቶክ ሸቃዮቻቸው አማካይነት የተመደቡበት ሃቅን የመሸፈን ተልዕኮ ሲያከናውኑ መደበቅ ከማይችሉበት ደረጃ በመድረሱ ይኸው ዛሬ ከአዲስ አበባ ተሻግሮ ችግሩ ወደ ትግራይም ጭምር በመሸጋገሩ የትግራይ ነጋዴም ሌሎቹ የቀመሱትን ጅራፍ መቅመስ ጀምሯል።በዚህ የውሸት ተልእኮ ለማካሄድ በትግራይና በውጭ አገር የተመደቡ የወያኔ የዜና ማሰራጫ ሸቃዮቹም አፍረው በመሸማቀቅ ይህ ካቅማቸው በላይ የተከሰተው ዱብ ዕዳ ዋሽተው እንዴት መከላለከል እንደሚችሉ አዲስ የውሸት ስልት ከጌቶቻቸው እየጠበቁ ይገኛሉ። ወያነ ትግራይ የኮሚኒስቶች ፍልስፍና አነግቦ መሬት በቁጥጥሩ ሥር አስገብቶ ሸቀጡን፤የመገናኛ አውታሮችን፤ ባንኮችና ንግድ ቤቶች በአስመጪና ላኪ በዋናነት ሃብታም ነጋዴ ሆኖ ለጥቂቶች ገነት ለብዙሃኑ የጭንቀት ኑሮ የሆነ ሥርዐት መሥርቷል።ሸማቹና አምራቹ በወያነ ትግራይ ዋና ታጁርነትና ቁጥጥር ስለሚገራ የዚህ ታጁር ተመፅዋች እና ትዕዛዝ አክባሪ ከመሆን አላለፈም። ታጁሮቹ ካቅም በላይ በሚጋብሱት ሃብት ሲተፉ ስለሚያድሩ ትፋታቸው የገባየው ዓየር በክሎታል።ምሕረት የለሽ ነጋዴ ቢፈጠርም የተማረው ከሥርዓቱ ነውና ተወቃሹ ነጋዴው ሳይሆን በዋናነት ሥርዓቱ ነው። በዚህም የተነሳ የገበያው ንረት ሲታወክ ስርዓቱን የሚመሩት ጥቂት ወረበሎችና አማካሮቻቸው “ደርግ” ሲያደርገው እንደነበረ የዋጋ ቁጥጥር ስልት ተከትለው ይኸው ዛሬም የዋጋ ንረት መነሻ ምክንያቱን በነጋዴው ላይ በማመካኘት አንዱን ሲቋጥሩ አንዱን ሲፈቱ ይታያሉ። ሥርዓት በዘመናዮቹ የወያኔ ትግራይ ያዲሱ ትውልድ የመሳፍንቶችና ጫካ በቀል ከብረቴዎች ስበስብ የሚመራ ስለሆነ እነኚህ መሳፍንቶች የሚከተሉት ሞራላዊ እሴት ቅጥፈት ሲሆን፤- ቅጥፈት ደግሞ“ በአገራችን ሞራላዊ እሴት ብቻ ሳይሆን የሥርዓተ መንግሥቱም ዋልታና ማገር ሆኗል። (In our country the lie has become not just a moral category but a pillar of the state) (ሰውነት መልካሙ) የዓለም የኖቤል ሽልማት ተሸላሚና የቀድሞ ሶቭየት ሕብረት ሥርዓተ -መንግሥት ነቃፊ ከነበሩት አለክሳንደር ሶልዘንስቲ ንግግር የተወሰደ።) <ስለሆነም ከትግራይ ጫካ የተሰጠን መንግሥት የሚከተለው ሞራላዊ እሴት “ቅጥፈት” ስለሆነ ቅጥፈትም የሥርዓቱ ዋልታና ማገር ስለሆነ በፖለቲካውም ሆነ በምጣኔ ሃብቱ በኩል በሕዝቡ ላይ የሚደረሰው የስቃይ ንዳድ ሲጨምር ሥርዓቱ የሚይዘውና የሚጨብጠው እያጣ አንዱ ሲቋጥር አንዱ ሲፈስበት ተጨንቆ ይታያል። አንዱ ሲቋጥር አንዱ እየፈሰሰበት ተቸግሮ ያለው ይህ ዝርክር ሥርዓት በተቃዋሚ ሃይሎች መወገድ አልቻለም። ይህ ከጫካ የተሰጥን መንግሥት የሚወገደው ዕጣ ፈንታችን ሆኖ “ባንድ አጉራ ዘለል ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት እንደሚሆን” ስጋቴ እየጨመረ ሄዷል። ሰላም እንሰንብት። ጌታቸው ረዳ Getachew Reda editor Ethiopian Semay www.ethiopiansemay.blogspot.com

Friday, January 14, 2011

TPLF the Cosa Nostra (MAFIA) of Tigray

ይድረስ ለጎጠኛው መምህር (አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ ( ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com\ TPLF the Cosa Nostra (MAFIA) of Tigray 1/14/11 By Getachew Reda Ethiopian Semay www.ethiopiansemay.blogspot.com

Did you visit Aigaforum.com today? The Meles Zenawi propaganda crew calling itself “ Aigaforum.com” based here in San Jose, have posted a clip of picture showing some dozen of people in Addis Ababa (perhaps visitors from the Diaspora) sitting in a round table enjoying “Beer Draft” somewhere in the reserved hotels only for the special class and the servants of the Cosa Nostra system in the corrupted TPLF manipulated market system as a sign of progress, where neocolonial Ethiopia of TPLF era where colonialists and foreign land grabbers are legally allowed to seize Ethiopian vast lands for 90 years in the name of investment in a form of "contract", in a country where few snatch and collect the wealth through power, gun/intimidation, ethnic and political affiliation are now trying to show a clip of Beer Draft drinkers depicted as symbol of wealth and progressive economy and freedom is indeed ignorance of Ethiopian life if not a sign of sickening soul. These lost soul are indeed sick to their head for telling us how Ethiopia is enjoying freedom and growing richer just because as the Derg era society used to drink Beer Draft while the horrendous red terror is throwing dead body on the door passage of the hotel where they blindly enjoying drinking their beer Draft. The Derg media used to show the same clip on magazines, how members and families of Farmers’ Associations enjoy drinking beer for the first time in Ethiopian history. Now, history is now repeating itself. Are these propagandists little kids or what?
Do you remember on the campaign trail in 2008, Obama told Joe Wurzelbacher, who became known as Joe the Plumber, that "if the economy is good for those at the bottom, it's going to be good for everyone". At the same talking, does that reality for the bottom class show good standard living in Ethiopia when the Aiga poor souls post a picture of Beer drinkers representing the poor?
Check the pictures above Ethiopian mothers, young, elders, children starved to death looking some left over from the city collected toxic garbage which the Meles Zenawi/TPLF propaganda crew hide from you and compare the picture that the Meles propaganda crew posted it on their website as if Ethiopians are getting rich which showed a handful Diaspora visitors or the system’s cadres or few fortunate who got help from the Diaspora support every month some few Dollars through Western Union for their evidence. Finally, for us to laugh at them, these lost sheep herded by Meles Zenawi’s wrote the following laughable script under the picture they posted it to show how Ethiopia is getting rich for drinking “Draft Beer” as a sign of richness! Here is what they said to us Extremist may not believe when we say there is a new Ethiopia but the world is noticing! It is their loss to miss such transformation of their beloved mother land!" Isn’t that laughable?
These chaotic TPLF, these jungle terrorists who tortured our parents, popular elders, families in massive and citizens with live fire, these Mafiosi got a nerve to call the opposition Diaspora Extremists? Please do read my previous article “Who is extremist?” posted on Assimba.org or just Google it “who is extremist!? I have read many lie and disinformation, but never seen or read like TPLF's. They are strange, when they lie, they simply bring to link and colide the sky with the earth as long as it serve them or cover their mission. Ethiopian should pray to be releaved soon from these Cosa Nostra of Tigray. By Getachew Reda/------Editor Ethiopian Semay

Wednesday, January 12, 2011

Ethiopia Takes Punitive Action against EPDP January 3rd, 2011

ድረስ ለጎጠኛው መምህር (አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ ( ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com http://www.ethiopiansemay.blogspot.com

Ethiopia Takes Punitive Action against EPDP

January 3rd, 2011

Reports out of Addis indicate that the Ethiopian government slashed in half the financial support it was providing the Eritrean Democratic People’s Party (EPDP). Many expected such action but are expressing concern about the safety of those who oppose the conference or the coming congress. It is to be remembered that the Ethiopian radio Wogahta had publicly threatened anyone who opposed Ethiopia’s agenda. The EPDP was receiving 15-20,000 birr per month. The Afar movement is paid up to 150,000 Ethiopian birr per month while the Kunama organization receives 85,000 Eth birr. The others are paid between 15-25,000 Ethiopian birr each. Each member of the EDA executive committee is paid 3,000 Ethiopian birr per month. At present Bashir Ishaq, Kernelios Osman and Amha Domenico are considered employees of the Ethiopian state and are paid salary and benefits in full, equal to any other Ethiopian government employee.

Posted in ALL HORN OF AFRICA NEWS, Eritrea, Ethiopia

Friday, January 7, 2011