Wednesday, November 30, 2011

ሰንደቃላማችን በስያትል ባንዳዎች ለድርድር ቀረበ!


To see the page/font with a wider range, please press the key Ctrl and + sign. To view the page/font with a narrow range, please press the key CTRL and _ sign.

የሚታየው የወያኔ ገበና ማህደር አዲሱ መጽሐፍ ለመግዛት $30.00 ዶላር ሲሆን ይድረስ ለጎጠኛው መምህር መጽሐፍ ደግሞ $25.00 ወይንም ሓይካማ የሚለው የትግርኛ መጽሐፌ ደግሞ $15.00 ዶላር ብትልኩ መጽሐፎቹን ማግኘት ትችላላችሁ።Getachew Reda P. O.Box 2219 San Jose, CA 95109 getachre@aol.com Phone (408) 561 4836

ከሃዲ ባንዳዎችን ራስ ሙሉጌታ እንዲህ ነው የሚያደርጓቸው።”
ከማቀርብላችሁ ታሪክ የተቀነጨበ።


ከላይ የሚታዩት ሁለት ፎቶ ግራፎች አክሱም ውስጥ ይገኛሉ። አንዱ አጼ ዮሐንስ የተናገሩት የአገር እና የሰንደቃላማ ትርጉም ሲሆን። ከዳገት ላይ የሚታየው ገዳም ከአክሱም ከተማ ሁለት/ሦስት ኪሎሜትር ራቅ ብሎ የሚገኝ ካሁን በፊት የደብሩ አስተዳዳሪ የነበሩት የኔ አጎት  ከነፎቶግራፋቸው በዚህ ድረገጽ ለጥፌው የነበረው የአባ መንጠሌዎን ደብር ነው። በገዳሙ የተቀበሩት እና የመቃብራቸው ሃውልቱት አሁንም በግልጽ ቆሞ የሚታየው ከተስአቱ ቅዱሳን አንዱ አባ መንጠሌዎን የመሰረቱት ገዳም ነው።

እንደ ምታዩት ገዳሙ የተመሰረተው በጣም ረዢም በሆነ ጫፍ ተራራ ላይ ስለሆነ፤ ልጅ ሆኜ ባዓሉን ለማክበር ከወላጆቼ ጋር ሄጄ፤ ብርዱ አይጣል ስለነበር፤ የአባታችን የእህት ልጅ (በወቅቱ ዲያቆን ገብረክረስቶስ) ከነበረው ጋር ሌሊቱ ያኔ ወደ መቅደስ አልሄድም ብየ በአባታችን መኖርያ ውስጥ ተኝቼ አድሬ (ሲቀደስ ብቻየን ቅዱሳን መጻሕፈቱ በተከማቹበት ቤት ብቻህን አትቅር ተብየ እምቢ ስላለሁ ተኝቼ በማደሬ ወደ ሦስት ሰዓት “ከንጋቱ/ሌሊት” ፀጥ ባለው አስፈሪ የገዳም ሌሊታዊ ፀጥታ ተኝቼ እያለሁ በገዳሙ  አድባር “ዓንደረቢ” ይሉታል ጉሮሮየ ታፍኜ አፌ ተዘግቶ በወቅቱ፤ የለፈለፍኩት የህጻንነት ፍርሃት ምን እንደገጠመኝ ሳስታውሰው አሁን አሁን ያስቀኛል/ይገርመኛልም።)  ጥዋት ሲነጋጋ ሰንደቃላማ እንድሰቅል ቀስቅሶኝ፤ በታዘዝኩት መሰረት ወደ ላይ ወጥቼ ስነደቃላማው ለመስቀል ገደሉ አፋፍ ላይ ስሞክር ድንጋይ አዳልጦኝ ወደ “አነስተኛው” ገደል  በመወደቅ ትረፍ ብሎኝ ባንድ ቋጥኝ ተቀርቅሬ በመትረፌ በሰዎች ተጎትቼ ስድን ሰንደቃላማዋ አንገቴ ላይ ከጠመጠምኩት ነጠላ ከነ እንጨቷ ተጠምጥማ ስለነበር እጄ ሳልይዛት እሷም አብራኝ ከገደሉ አደጋ መዳንዋ ሳስታውሰው አሁን የዛሬዎች ባንዳዎች ሰንደቃላማዋን አሳንሰው ሲመዝኗት ማየቴ አንጀቴ ይቃጠላል። ታሪክ በማሕደሩ እየዘገበን ይጓዛል፤እኛም አየተመዘገብን አብረነው አንጓዛለን።

ሰንደቃላማችን በስያትል ባንዳዎች ለድርድር ቀረበ!
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ድረ ገጽ)
አርዕስቱ ሰንደቃላማችን በስያትል ባንዳዎች ለድርድር ቀረበ! ወይንም በእንግሊዝኛው “ The Seattle Conspiracy” ብትሉት ቅር አይለኝም።
 ሌላ መነጋገርያ ርዕስ ትቼ ለዛሬ ይህን ሳቀርብ ይህ ፋታ ያልሰጠኝ ሁሉም አገር ወዳድ እና ለኢትዮጵያ ሰንደቃላማ የክብር ቦታ የሚሰጥ ዜጋ ሁሉ አበክሮ መከታተል ያለበት ጉዳይ ለማስገንዘብ ነው። በፈረንጅ አቆጣጠር Saturday November 12, 2011 በስያትል ከተማ ውስጥ በተሰባሰቡ ጠባብ ብሔረተኛ ግለሰቦች (ከትግራይ፤ ከኦሮሞ፤….ከመሳሰሉት ግለሰቦች) የተዘጋጀው ስብሰባ “የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ ለኦነግ ባንዳዎች ለድርድር ቀርቧል”።
ስብሰባውም ካሁን በፊት ከተደረገው ስብሰባዎች ሁሉ በጣም “ልዩ” ያደረገው አንድ  የስብሰባው አጀንዳ አድናቂ የሆነ ግለሰብ የሚከተለውን በድረገጸች ያስተላለፈውን አረፍተ ነገር ይመለከቱ። እንዲህ ይላል።
 By Kirubeal Bekele-  Seattle had its first Forum meeting last Saturday November 12, 2011. This meeting was highly anticipated mainly due to its unique nature of trying something new that has never been tried before.” እንግዲህ ልዩ ያደረገው ስበሰባው ባሕሪ የኢትዮጵያ አገራዊ ሰንደቃላማ  ለሽብርተኛው “ለኦነግ ባንዴራ” ለድርድር በመቅረቡ፤ ስብሰባው አዳራሽ ውስጥ ሁለቱም እንዳይውለበለቡ የተደረገበትን ባሕሪ ነው “ልዩ የሆነበት ምክንያት”።
በወቅቱ በተዘጋጀው ስብሰባ ተናጋሪ እንግዶች ተብለው የተጠሩ የክብር እንግዶች የግንቦት 7ቱ መሪ ብርሃኑ ነጋ እና የኦሮሞ ነጻ አውጪ ደርጅት ፀሐፊ አሚን ጃንዳይ ማለትም ሁለቱም ድርጅቶች በኢትዮጵያ/ትግራይ ሕዝብ ላይ ለፈጸመው ወንጀል ተፈላጊ በሆነው በኤርትራው “ሽብርተኛ” “ኢሳያስ አፈወርቂ” የሚደገፉ እና ሕብረት በተባለ ኢትዮጵያዊ ድርጅት ውስጥ የተካተተው የታንዱ ሊቀ መንብር አረጋዊ በርሐ ናቸው።
ሦስቱም እንግዶች ሲጋበዙ አዘጋጆቹ የተስማሙት አንድ አጀንዳ ነበር። አጀንዳውም “አዳራሹ ውስጥ የኦነግ ባንዴራ ካልተሰቀለ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቃላማም መሰቀል የለበትም በሚል ተስማምተው፤ በአያቶቻችን ደም ተከብሮ ወደ ጥንት ስፍራዋ በመመለስ በተባበሩት የዓለም መንግሥታት/አገሮች የክብር ስፍራ ተሰጥቷት በያገሩ አምባሲዎች እና ስብሰባዎች በክብር እንድትውለበለብ የተደረገቺውን የእናት አገር ኢትዮጵያ አርማ እንደ ማፈሪያ ጨርቅ እና እንደ ድርጅታዊ አርማ ተወስዳ እንዳትውለበለብ በመስማማት ሰንደቃላማችን በስያትል ባንዳዎች ለኦነግ ባንዴራ ሲሉ ለድለርድር አቅርበዋታል።
ከላይ የተጠቀሰው የባንዳዎች ሴራ በMeleket Ethiopian Radio: (ካናዳ ውስጥ የሚተላለፍ) በሚባለው ራዲዮን የተደመጠውን በኢትዮጵያዉያን ሃይሎች እና ለሻዕቢያ እና ለኦነግ ጥብቅና የቆሙ አዲስ በቀል የቅርብ አመት መጤ ባንዳዎች የተደረገው ውይይት ነበር ሴራውን ልናደምጥ የቻልነው።  (http://ecadforum.com/blog1/2011/11/28/meleket-ethiopian-radio-interesting-radio-discussion/)
ከላይ የተመለከተው የራዲዮ ውይይት የምታዳምጡት በሁለት ተጻራሪ ጎራ የተሰለፉ ወገኖች ስታደምጡ በተለይ በሻዕቢያ እና በኦነግ ፋሺስታዊ ፖለቲካ የተማረከ “ለሰይጣን ጥብቅና መቆም ባልተለመደው ዓለም ለዲያብሎስ ጥብቅና የቆምኩኝ/ዘዴቪልስ አድቮኬት ነኝ” “ኢትዮጵያ ሰንደቃላማ በሕዝባዊ የስብሰባ ላይ ቢሰቀል ባይሰቀል ጉዳዬ አይደለም” “ ሻዕቢያዎችን አጭበርባሪዎች አትበሏቸው! አጭበርባሪዎች አይደሉም!” “ሻዕቢያዎች በጉልበት አሸንፈውናል!”  ‘እገሌ ሲ አይ ኤ ነው … ምናምን የምትሉት ያፈጀ ያረጀ የድሮ ተረት ተረታችሁን አታውሩ…..” በማለት በኩራት እና በትዕቢት ያለ ምንም ማሰላሰል እና ማመንታት ሲደነፋ የምታደምጡት የ97ቱ ዓ.ም. ያዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሊቀ መንበር ነበርኩ የሚል “ሌሎቹ ሲጋፈጡ እሱ ግን ነብሱን ለማዳን  የተደበቀ ጮሌ”፤የግንቦት 7 እምባ አፍሳሽ እና ecadforum.com የተባለ ድረገጽ እና ፓል ቶክ አዘጋጅ የሆነው “ተክሌ” የተባለው ካናዳ አገር የቫንኩቨር ኗሪ ወጣት ከላይ የተመለከተው ማሕደር በመግባት በጥንቃቄ እንድታደምጡት እጋብዛለሁ።
ልጁ ጅላጅል ብቻ ሳይሆን ወላጆቹን፤ አገሩን፤ ሃይማኖቱን፤ሰንደቃላማውን ክብር ሲያጣጥል እና የሰንደቃላማ ክብር እና ከባድ ዙፋን አንደ ኳስ ጫዋታ የሸሚዝ ልውውጥ  ያክል በመመልከት ሲዘልፍ ነውር መሆኑን ብቻ ሳይሆን ጅላጅልነቱ፤ በጣም አደገኛ እና ባሕልንና ያገሪቱ ሰንደቃላማ ክብርን በማይገባ “አልትራ አናርኪዝም” (አክራሪ አጣጣይ) የፋሺሰቶቹ “ቀይሕ ዕማባባ” የወላጅ እና የአዛውንቶች ውጤት
የሚረግጥ ባሕሪ የተጠናወተው አደገኛ ኩታራ መሆኑን ትገነዘባላችሁ። የዚህ ልጅ አነጋገር እና የመለስ ዜናዊ ለሰንደቃላማ እና ያገር ክብር ያለው የዘቀጠ ንግግር ስታስተያዩት ልዩነት አታዩም። ለሚወዳት ፍቅረኛውም፤ ለአገርም፤ለሰንደቃላማም ምንም ክብር የማይሰጥ ተደራዳሪ እና አልትራ መሆኑን ትገነዘባላችሁ። መለስ ዜናዊ ኣእላፍ ሕዝብ አሰልፎ ለሞት የዳረገበትን የባድሜ መሬት “ከርስድ ላንድ” ብሎ ነበር የሰየመው። ቢሄድም ቢመጠም ጉዳየ አይደለም/ኢን ፕሪንሲፕል መሬቱ ለወራሪው ለሻዕቢያ እንዲሰጥ ተስማምተናል። ተግባራዊ ለማድረግ ደግሞ ‘አንወያይ” ነበር ያለው ያ ሁሉ ሰው ለሞት ዳርጐ። ተክሌ እና የሲያትል ባንዳዎችም የኦነግ ባንዴራ ካልተሰቀለ የኢትኦጵያ ሰንደቃላማም እንዳይሰቀል/እንዳይውለበለብ ከጠየቁት ጋር ተስማምተው ለድረድር ቀረቡ። ያውም “ጥይት ሳይጮህባቸው”!
የዚህ ኩታራ ድፍረት መጠን ከማለፉ የተነሳ “ካረንት አፈይርስ/ኢካዴፍ” በሚባለው ጸረ ትግራይ ዘመቻ በሚካሄድበት የፓል ቶክ/ራዲዮን የሚኩራራ ወጣት መሆኑን አትዘንጉ።ይህ ድፍረት እንዴት እና በእነማን አመካይነት እየተከናወነ እንደሆነ ታሪክ እየዘገበው ነው። ታሪኩ ደግሞ በድምጽ መቅጃ እየተዘገበ ይገኛል። ወጠቶቹ የባንዳ ቃላቸው እና አቋማቸው በየሄዱበት አንደ እነ መለስ ዜናዊ እና ኢሳያስ አፈወርቂ እንዲሁም እንደ እነ ሌንጮ ለዘላለሙ በሕዝብ ጀሮ እየተደመጠ ይኖራል። ሲያረጁም ያፍሩበታል። የጥቁር ሕዝቦች አርማ በመሆን ወድቃ የተነሳቺውን ሰንደቃላማችን ዳግም በዓለም አደባባዮች እና አዳራሾች አንድትውለበለብ  ወላጆቻችን ከጣሊያን ወራሪዎች እና ባንዳዎች ጋር ያደረጉት ግብግብ ዳግም እንዲመለከቱት በዚህ ድረገጽ ዛሬም በድጋሚ ልብ እንድትሉት እጋብዛችለሁ።
የሲያትል ባንዳዎች እና የግንቦት እና የኦነግ ባንዳ ጭፍራዎች ወላጆቻችን ያሳለፉት መራራ ሕይት እና ግብግብ፤ የተባበሩት መንግሥታት የማያውቀውን “የፈሺስቶች የኦነግ የድርጅት ባንዴራ” ዓለም ካወቀው እና አፍሪካኖች እና ጃማይካኖች በሚኰሩበት ብሐራዊ ሰንደቃላማችን ለድርድር ማቅረብ ታሪክ የማይረሳው አስቀያሚ የፖለቲካ ንግድ በመሆኑ በዚህ አሳፈሪ ሴራ የተሳተፉ እያንዳንዱ ባንዳ ከታሪክ እንዲማር ከዚህ ቀጥሎ ያለውን የባንዳዎች ቅጣት እና የወላጆቻችን ቆራጥ አቋም እነሆ። ባንኩቨር ወይንም ሲያትል እንጂ ኢትዮጵያ ውስጥ አንኖርም እና የሃገር አርማ መድፈር እንችላለን የምትሉ ወይንም ከኢትዮጵያ ሰንደቃላማ ጋር የተፈራረምነው ውል የለም የምትሉ ባንዳዎች ሁሉ እናንተ ካልፈረማችሁበት ወላጆቻችን በድረድር ሳይሆን በደማቸው ፈርመው የዓለም ሕዝቦች ፤መስጊዶች፤ቤተ መቅደሶች፤ገዳማት፤መካነ መቃብሮች፤ አደባባዮች፤ ሰማዩ፤ኮዋክብቱ፤ እእዋፋት እና አራዊቱ ሁሉ እንዲያከብራት አድርገዋል። አናከብርም ብሎ ከጠላት የተሰለፈ ወይንም የሰንደቃላማን ክብር ዝቅ ያደረገ፤ የዘለፈ፤ያንቋሸሸ፤ለድርድር ያስተናገደ፤ “ባንዳ” ምን ቅጣት ይደረስበት እንደነበረ የሚከተለው የታሪክ ቅጣት እንድናስታውሳችሁ ተገደናል። የነዚህ ሰዎች አገር የማፈራረስ ስልት የሚከሽፈው ዛሬም እንደ ትናንቱ ባንዳዎች ፊት ለፊት ካልተጋፈጥናቸው እንደ እነ ሻዕቢያዎች እና ወያኔዎች የመቶ አመት ታሪኩ ግብግብ ብቻ ሳይሆን እየደረሰን ያለው “ሰንደቃላማችንም ጭምር ለድርድር ቀርቦ እንዳይውለበለብ የማድረግ ዘመቻው ወዴት እያመራ እንደሆነ መገንዘብ አያዳግታችሁም የሚል እምነት አለኝ።
የሚከተለው ታሪክ የተገኘው ዶ/ር ተስፋዬ መኮንን ባይለየኝ የተተረጎመ “ቀይ አምበሳ” ከተባለ ለኢትዬጵያን ሰንደቃላማ እና የነፃነት ክብር ብሎ ሲጀመር እስኪጨረስ ከ1928 .ም በጣሊያን ወረራ የተደረገው የመከላከል ውጊያ ተካፍሎ ለኢትዮጵያን ክብር የቆመ ኩባዊው ኮሎኔል አሊሃንድሮ  ዴል ባዬ በዓይኑ የተመለከተውና በጦርነቱ የተሳተፈበት ትዝታ በጻፈበት መጽሐፍ የተቀነጨበ ታሪክ ነው። ታሪኩ ረዘም ቢልም ታግሳችሁ አንብቡት። ሶፋ ላይ ተመቻችቶ ረዢሙን ታሪካቸው ለማንበብ ከሰለቸን ሕይታቸው አከላታቸው አጥተው “ኢትዮጵያዊ” ዜጋ የሚለው የምንኮራበት መታወቂያ ደብተራችንን እንድንይዝ ያደረጉትን የበጐ አድራጊ ወላጆቻችንን ገድል መናቅ እንዳይሆንብን እንጠንቀቅ። 
“ ………..በዚህ መንገድ ህይወት
አንድ ቀን ምሽት ወደ አርባ የሚጠጉ ጥቁር የቆቦ ጐሳዎች ወደ እኛ ሰፈር ተሳስተው ገቡ። ሀሳባቸው ከጣሊያን ጦር ጋር ለመደባለቅ ነበር። የእኛን ሰራዊት “የዱቼ” ሰራዊት ከሆኑት ከኤርትራ ተወላጆች ጋር በማመሳሰል በስህተት ነው የተደባለቁት። ስህተታቸውን ሲያውቁት እጅግ በጣም ዘግይተው በመሆኑ ወደ ወደ ላ ሊመልሱት አልቻሉም።
ራስ ሙሉጌታም ወደ አሉበት ቦታ እንዲመጡ አስጠሯቸው። በጥሩ አቀባበልና በተለሳለሰ መንገድ ያነጋግሯቸው ጀመር።
“ለምንድነው ከጣሊያኖች ለማበር የምትሄዱት?”
እነዚህ አሳዛኝ የሆኑ የቆቦ ተወላጆች በፍጹም እውነተኝነት እንዲህ ሲሉ መለሱ።
“ጌቶች! ምክንያቱ ለእያንዳንዳችን ጠመንጃ በየወሩ 20 ታለር የእነሱን ገንዘብ ስለሚሰጡን ነው።”
“20 ታለር ጥሩ… እኔ ደግሞ 20 ጅራፍ እሰጣችለሁ። እኔ ግን በየቀኑ ነው።”
ያሉትን ፈጸሙት። ሁልጊዜ ጠዋት ጠዋት ብዙ ከፍተኛ ሥነ ሥርዓት እየተደረገ እስረኞቹ እየተሰበሰቡ በዚያች የአለንጋ ግርፍ ይተለተሉ ነበር። ለብዙ ቀናት ቁስላቸው እስኪገጥምና እስኪጠግ ድረስ ይተዋአቸውና እንደገና ሌላው ዙር የአለንጋ ግርፍ ይቀጥላል። እንዲህ እያለ ጨዋታው ሲቀጥል ሌላው አይነት የቅጣት አይነት ተፈፀመባቸው። አፍንጫቸውን፤ እጃቸውን፤ጆሯቸውን፤ምላሳቸውን፤ከንፈራቸውን ቀስ እያሉ ተራ በተራ ቆረጧቸው። አንዱን የሰውነት ክፍል ከቆረጡ በ እንዳይሞቱ ያክሟቸዋል። ሲጠግግ ሌላውን ይቆርጣሉ። የመጨረሻው የተደረገው በመጨረሻው ቀን በአንድ በጋለ ብረት ፊታቸው ላይ ምልክት ጠባሳ ማድረግ ነበር። ይህ ደግሞ ከሃዲ ለመሆናቸው መለያ እንዲሆን ነው። እናም ብዙዎቹን ዲዳ፤ ዓይነስውሮች፤ እጅ አልባ፤አፍንጫ ቆራጣ አስቀያሚ ገፅታ ይዘው አንድ መልዕክት የያዘ ፅ ሑ ፍ አሲዘዋቸው ወደ ጣሊያኖቹ መስመር መሄጃ መንገድ ላይ እንዲቀመጡ አደረጓቸው። የፅሑፉም መልዕክት እንዲህ ይል ነበር።
“ከሃዲ ባንዳዎችን ራስ ሙሉጌታ እንዲህ ነው የሚያደርጓቸው።”
ደራሲው ኮሎኔል አሊሃንድሮ ስለ ቅጣቱ አስመልክቶ እንዲህ ይላል፡-
“ በበከሌ እንዲህ ያለው ነገር እንዳይፈፀም ተቃዉሜአለሁ። ምክንያቱም እጅግ ዘግናኝ አሰቃቂ ቅጣት ብቻ መሆኑ ሳይሆን እንዲህ ላለው ነገር ማረጋገጫ የጣልያን መንግሥት ካገኘ በኢንተርናሽናል ሊግ ኢጣልያዎቹ አጋጣሚና ተሰሚነትን ሊረዳት ስለሚችል ነው።ራስ ሙሉጌታ ግን አፍጥጠው፤
ለእኔ ኢንተርናሲዮናልና አንድ የሞተ ጅብ አንድ ናቸው። ሁሉም አገሮች አቢሲኒያን በመቃወም ሊሰለፉ ይችላሉ። እኔ ግን ሁሉንም ላሸንፋቸው እችላለሁ። ከፈለጉ ሁሉም ፈረንጆች ይምጡ ልንሸነፍ አንችልም! ልንሸነፍ አንችልም፤ ገባህ!?”
ራስ ሙሉጌታ ማታ ማታ ስለ ጦርነት ድርጊታቸውና ውሎአቸው በጐራዴያቸው ነጮችን እንዴት እንደቆራረጡና እንደገደሏቸው ሲተርኩ ያመሻሉ።
በእነዚህ ቀናት በአንዱ ከራስ ካሳ አንድ መልዕክት ደረሰን። የጥቁር ሸሚዝ ለባሾች ከፍተኛ የጦር ቡድንን ከብበው እንደሚገኙና ለማጥፋትና ለማሸነፍ ወሳኝ በሆነ መልኩ ለመግጠም ተጨማሪ ሀይል እንደሚያስፈልጋቸው ነበር የጠየቁን። በተለይ እንድንሰጣቸው የጠየቁን በዚህ በጦርነቱ ላይ የሁሉን ኢትዮጵያዊ ቀልብ የሚስበውንና ሁሉም እንዲኖረው የሚፈልገውን ፀረ አውሮፕላን መትረየስ በመድፍ ሆነ በዘመናዊ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ለሚደረግብን ጥቃት ለመከላከሉም ሆነ በማጥቃቱ ወቅት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስለሚሰጥ በጣም ተፈላጊ ስለነበር ነው። ራስ ሙሉጌታ ጓድ “ዶኒ ኦዳዩን” እና  እኔን ወታደሮቻቸውንንና ለውጊያ የሚያስፈልጉንን ቁሳቁሶች ሁሉ ይዘን እርዳታውን እንድናደርግ አዘዙን። ዝግጅታችንን ጨርሰን ጉዟችንን ልንጀምር ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩን ልጃቸውን ታደሰን ጠርተው ከእኛ አገር እንዲደባለቅ አዘዙት።
“እነኝህ ውሾች ፈረንጆች መያዝ አለባቸው። አንድም በህይወቱ ወይም ጤነኛ ሆኖ መቅረት የለበትም።” አሉን።
ሊመሻሽ ሲል ጉዟችንን ጀመርን። ድቅድቅ ያለ ጨለማ ሙሉ በሙሉ ፀጥ ባለው ሰፈር ሲሰፍንና ሌሊቱ እየጠለቀ ሲሄድ ከወታደሮቻችን ጋር ወደ ሞት ወይም ወደ ድል አቅጣጫ ወደ ጠላት ሰፈር መሬት ለመሬት መሳብ ጀመርን። ሊነጋጋ ሲል ራስ ካሳ በያዙት ስፍራ ደረስን።
ቀዳሚ ጦራቸው ወደ ብልህ አለቃቸው ድንኳን ድረስ ይዘውን ሄዱ። ራስ ካሳም ጠላትን ከብበው በሚገኙበት ከፍተኛ ተራራዎች ላይ ከሚገኙት የተፈጥሮ ዋሻዎች ሆነው የ “ዱቼ” አገልጋይ ወታደሮች የያዙትን ቦታ ያሳዩን ጀመር።
…….. ይህ በእንዲህ እንዳለ በቡድን እየተከፈለን በተራሮቹ መሀል በተለያየ አቅጣጫ ቁልቁል መውረድ ጀመርን። እነኛ የኢትዮጵያ ልጆች ቁልቁል ሲወርዱ ጐራዴያቸውን መዝዘው አየሩን እየቀዘፉ በመንገዳቸው ላይ ሲጓዙ በጣም ያስፈሩ ነበር። ክፉኛ የተደናገጡ ጣልያኖች እውነተኛውን የሽንፈት ፊት ለማሳየት ሁለት እጆቻቸውን ወደላይ እያነሱ ያለምንም ጥርጣሬ የራስ ካሳ ወታደሮች ቃል በገቡላቸው መሰረት የጠየቁትን እንደሚያደርጉላቸው ባለመጠራጠር በሙሉ ተማምነው ነበር። ሆኖም ግን ቀዳሚዎቹ የጣልያን ጥቁር ሸሚዝ ለባሾች የመጀመሪያው መስመር ላይ እንደደረሱ ያ ዘግናኝ ጐራዴ እላያቸው ላይ ጭንቅላታቸውን በመፍለጥ እጆቻቸውን በመቁረጥ አንጀታቸውን በማውጣት ጀመሩ። በዚህ ዘግናኝ ጥቃት የተደናገጡት ጣልያኖች ለዚህ መጠነ ሰፊ ለሆነው ምላሽ ለመስጠትም ቢፈልጉ በፍፁም አይችሉም። ጊዜ አልነበረምና። ይህ ድንገተኛ የሆነ ጭፍጨፋ ለሁለት ሰዓት ያህል ቀጠለ። በመጨረሻም የ8000 ነጮች ሬሳ አንዱ በአንዱ ላይ ተነባብሮ  ምድር ደም ለብሶ፤ የነበረው እንዳልነበረ ሆኖ ቀረ። ውጊያው ፊት ለፊት ጨበጣ ለጨበጣ ነበር። 40,000 ኢትዮጵያውያን ጦረኞች ተሰልፈዋል። ያንን የሚጠሉትን ወራሪ ፊት ለፊት በጨበጣ ውጊያ ስጋ ለስጋ በመግጠም ፈጅተውታል።
አንድ የጣልያን ሻምበል ብቻ ከነ ህይወቱ ይዘዋል። እሱም ቢሆን በታደሰ ሙሉጌታ (የራስ ሙሉጌታ ልጅ ነው) ነው። ታደሰም ከነ ህይወቱ  ወደ ራስ ካሳ ዘንድ እንዲያቀርቡት አዘዛቸው። ጦሮኞቹ ከጦሩ ፊት ልብሱን አስወለቁት። የሰሜን ተራሮችን እየቧጠጠ እስከ አለቃቸው ድንኳን ድረስ እንዲጓዝ አደረጉት። ከጫካው በቆረጣቸው ልምጮች እየገረፉ በዚህ ባልታደለ ነጭ ሰው ቆዳ ላይ ቀይ ሰንበር እያወጡ ነዱት። የጥቁር ሸሚዝ ሻምበል መስዋዕትነት አስፈሪ ሆነ። አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንዳልነበረ ሆነ። አንገቱ ተቀላ። የንጉሱ ወታደሮች ለልዩና ለተከበሩ እስረኞች የሚጠቀሙበት የመግደያ ዘዴ አንገትን ሙሉ በሙሉ ሳይቆረጥ መተው የጣልያኑ ሻምበል እድል ሆኗል። ሻምበሉ ቆዳው ላይ በግርፍ በተፈጠሩት ከመቶ በላይ በሚደሙ ቦታዎች ብዙ ደም ስለፈሰሰው ከአንገቱ የፈሰሰው ትንሽ ነበር። ምንም ሳይናገር፤ምንም ብሶቱን ሳያሰማ ከራስ ካሳ ፊት ወደቀ። ዓይኖቹ ነጥተው እርቃነ ስጋውን እንደተጠቀለለ ስጋ ተጠቅልሎ ደም ተፍቶ ወድቆ ቀረ። ለእሱ በጣም ከፍተኛ የሆነ ሀዘን ተሰማኝ። ምንም እንኳን መጀመሪያ የሰራው ስራ የሚያዋርድ መስሎ ቢታየኝም በላ በጣም አዘንኩለት። ያንን ዳገት ሽቅብ ሲወጣ በሚያሳዝን ድምፅ እየጮኸ ይለምን ነበር። በንጉሱ ሰራዊት ውስጥ እያለፈ ሲሄድ በሚያሰማው ፍርሃትና ሃፍረት በጣም ተሸማቋል።
“እባካችሁ አትግደሉኝ አትግደሉኝ። ተገድጄ ነው ለመዋጋት የመጣሁት፡ እኔ ለአቢሲኒያን እዋጋለሁ። ወደ ጣልያን መስመሮች ላልመለስ ቃል እገባለሁ። ከእናንተ ጋር አብሬ እዋጋለሁ። ጣልያን እወጋለሁ፤ እትግደሉኝ።” የመጨረሻዎቹ ቃላተች ነበሩ።
ከጭፍጨፋው በላ ባለ 101 እና ባለ 105 ሚ.ሜ መድፎች፤ 200 የነፍስ ወከፍ መትረየሶች አንድ ሺህ ጠመንጃዎች፤ ብዛት ያላቸው ቦምቦች፤ፈንጂዎች፤ብዛት ያለው ምግብ፤5ሺህ የውጭ አገር የንግድ ምልክት ያለው ከጦርነት ለኔ ስጦታ የሆኑ ሲጋራዎች አግኝተናል፤ወርሰናል።
…. ቀኑ በፍጥነት መሸ። ጨለማውም ምድሩን ነከሰ። ዘማቾቹ ድላቸውን ማክበር ጀመሩ። ያገኙትን ድል ሰንደቃላማቸውን እያነሱ በሽለላቸው፤በፉከራቸው፤ በጭፈራቸው፤ያደምቁት ጀመር። በዚያ ሸለቆ ውስጥ  የተጋደመው ሬሳ ከምድር ላይ ለብርሃን ማረፊያ እንኳን አትገኝም።ሁሉም በኢትዮጵያ ጦረኞች እነኛን ሙታን ሙሉ በሙሉ በእነዚያ በልዩ የቀዶ ጥገና ማሳሪያቸው (እዚህ ላይ የደራሲው አገላለጽ ጐራዴያቸው ማለቱ ነው) አገለባበጧቸው፤ የጦርነት ድል መግለጫቸውን፤የወንድነታቸውን ምልክት ያንን ትኩስ የሰውነት አካል ሸልተው ጦራቸው ላይ ሰክተው ይዘውታል፤፡
ራስ ካሳን በሚገኙበት ቦታ በጦር ሰፈራቸው ጐበኘናቸው።
“ለምን አስከሬኖቹ እንዲቃጠሉ አያዙም? ሁሉንም ሰብሰቦ አንድ ቦታ ማቃጠሉን ይመረጣል። ሽታው ይወገዳል። ከአስከሬኖቹ ሊነሳ የሚችል ተላላፊ በሽታ ማስወገድ ይቻላል።” ብለን ጠየቅናቸው።
ራስ ካሳም በመገረምና ትካዜ በሞላው ፊት ትኩር ብለው ያዩኝ ጀመር።
“የጦረኞች ገላ አይበሰብስም፡ የሚቃጠለው ገላ ከእግዚአብሔር ጋር የተቆራኘው ብቻ ነው። እንዴት እነኝህ እርኩስ መጤዎች አቃጥላለሁ?”
….በሬሳ ሽታ በዚያ ቦታ ለመተንፈስ እንኳን አስቸጋሪ ሁኔታ ስለተፈጠረ የግድ መልቀቅና ወደ ተራረው መውጣት ተገደድን። ጅብና ጥንብ አንሳ አሞራው ያንን የሙታን ገላ ይቀራመቱት ጀመር።…….የ8000 ጥቁር ሸሚዝ ሰራዊቱ የገጠማቸው እድል “የዱቼን” ጦር እንደ ውስጥ እግር እሳት ስላንገበገበው የመልሶ
ማጥቃት ዘመቻው ከሦስት አቅጣጫ በተመሳሳይ ሰዓት በከፋ መልኩ ጀመሩ። …….ከሦስት ቀን አስከፊ የአንገት መቅላትና የጨበጣ ውጊያ በላ የራስ ካሳ በሰፈረበት ጦር ከሰፈረበት ብዙም ያልተከለለ ቦታ እረፍት በማድረግ ላይ እንዳለን ልክ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ሊነጋጋ ሲል መደበኛው የጣሊያን ጦር በተለያዩ የኤርትራ ተወላጆች ከተገነቡ የጦር ክፍሎች ጋር በመሆን የማጥቃት ዘመቻ በድንገት ሰነዘረብን። ውጊያውም ቀጠለ…….”
በማለት የኢትጵያ ሰንደቃላማ እንዳትውለበለብ ለማድረግ የጣረው ወራሪው የዱቼ ጦር እና  ያገሪቱ ዜጋ ሆነው ለሰንደቃላማይቱ ክብር የሌላቸው ተባባሪ ባንዳዎቹ፤ ከኢትዮጵያ አርበኞች ጋር የተደረገው ግብ ግብ ይህን በሚመስል አሰቃቂ ገድል በተሞላበት የመከላከል ጦርነት ተደርጐ ሰንደቃላማችን እንድትውለበለብ ያደረጉትን የወላጆቻችን የገድላቸው አርማ እና መመኪያ በማራከስ ፤ ዛሬ በምናያቸው የዘመናችን አመኬላዎች ሰንደቃላማችን  ለኦነግ ክብር ሲሉ በሕዝብ ስብሰባ እንዳትውለበለብ በማውረድ አሳፋሪ የባንዳዎች ስራ የፈጸሙ  የሲያትል ባንዳዎች እና ካናዳ ቫንኩቨር የሕግ ተማሪ ነኝ የሚለው “ተክሌ” እያለ ራሱን የሚጠራ የግንቦት 7 እና የሻዕቢያ አወዳሽ በካሃዲነታቸው ታሪክ ያስታውሳቸዋል። ለዚህ አሳፋሪ ድርጊታቸው ለኢትዮጵያ አርበኞች ማሕበር እና አገር ወዳድ ሽማግሌ ማሕበሮች ይቅርታ ካልጠየቁ፤ ድርጊታቸው መወገዝ አለበት።
ቃላችን አሁንም ትናንትም ወላጆቻችን በደማቸው ፈርመው ያስረከቡን ሰንደቃላማችን ለኦነግ፤ ለኦጋዴን ሶማሊ ተገንጣይ ቡድን ወይንም ለማንኛውም የፖለቲከካ ቅጥረኛ የድርጅት አርማ ለማስደሰት ብለን ብንሞትም ለድርድር አናቀርብም! ሰንደቃላማችን ከወደቀበት አንስተው የትም ቦታ እንድናውለበልባት ያስረከቡን የወላጆቻችን የአደራ ቃል እንጠብቃለን!!! ወያኔ በሰንደቃላማችን ላይ “ሰማያዊ ቀለም” ለጠፈባት ብለን ስናማርር የባሰውኑ “ከነጭራሹ ደብቋት” የሚሉ ደግሞ መጡብን። ወይ ኢትዮጵያ አገሬ አትሰሚው የለ! የራስ ሙሉጌታና የራስ ካሳ ፤የአርበኞቻቸው አጥንት ይውጋችሁ! መለስን ባንዳ እያሉ ሲሰድቡት ከርመው ተመልሰው እራሳቸው ሰንደቃላማችንን አውርዷት የሚሉ የባሱ ባንዳዎች ሆነው ቁጭ አሉብን እኰ!።ወይ ጉድ! ወይ አገሬ በውርጋጦች እንዲህ ተዋረድሽ?  አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ (www.ethiopiansemay.blogspot.com     getachre@aol.com   ( 408) 561 4838





Monday, November 21, 2011

ውሸታሞቹን ስንት ጊዜ ይማራችሁ እንበላቸው?




Dear Readers;
  I want all of you to visit Ethioforum.com and read on Hayelom Araya’s death on the commentary page and see for yourself how the ESAT TV (executive member) and EMF chief editor allowing Tigrayan people to be insulted by psychopathic individuals while he crossed the word I use (fool) in response to the same person use the same word (fool) while Kinfu Assefa allowed the word “fool” to be used to insult Tigrayans. I will have a full follow up on this next week, stay tune.  
A message to all Tigrayans; (from Ethiopian semay Editor)
  As you know well, we are challenging the bad system of TPLF not our people. But, there are few Ethiopian journalists like Kinfu Assefa the Ex member of the Army during the Derg  
currently living in Amsterdam/Holland and his associates may be Dawit Kebede  also a former Derg Army.( my apology if he is not EMF’s associate at this time- he has to come out and tell us he is not in EMF website as associate editor) who are in the business of bias journalism against Tigrayans. So you know now, based on the two time recent evidence I showed you, shows that there are bias and racist journalist in the opposition that they hate Tigrayans not Meles or TPLF or no body. That was their intention, their intention is by any means using EPLF/OLF supporters acting as  Ethiopians allowed to insult Tigrayans to be down graded on EMF.  And we Tigrayans and other Ethiopian patriots  will not allow that! we have to stick together when bias journalist like Kinfu and his friends target us when it comes against ourselves and our people in the name of politics.


 There is no point of me to expose TPLF when it insult the Amhara population, and not fair if I shut my mouth when journalists conspired with racist individuals to insult Tigrayan population to be insulted. We have all kind of enemies inside us, masquerading as political opposition and opposition media.

           Thanks Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay) read Kinfu Assefa’s website EMF on the following address
http://ethioforum.org/?p=9025#comments



To see the page/font with a wider range, please press the key Ctrl and + sign. To view the page/font with a narrow range, please press the key CTRL and _ sign.

 የሚታየው የወያኔ ገበና ማህደር አዲሱ መጽሐፍ ለመግዛት $30.00 ዶላር ሲሆን ይድረስ ለጎጠኛው መምህር መጽሐፍ ደግሞ $25.00 ወይንም ሓይካማ የሚለው የትግርኛ መጽሐፌ ደግሞ $15.00 ዶላር ብትልኩ መጽሐፎቹን ማግኘት ትችላላችሁ።Getachew Reda P. O.Box 2219 San Jsoe, CA 95109 getachre@aol.com Phone (408) 561 4836

ውሸታሞቹን ስንት ጊዜ ይማራችሁ እንበላቸው?ጌታቸው ረዳ (www.ethiopiansemay.blogspot.com) getachre@aol.com
ባለፈው ሰሞን “የሻዕቢያ ገበና እና ኢትዮጵያውያን ተቃዋሚ ድርጅቶች” ክፍል ሁለት አቀርብላችኋለሁ ብየ ነበር። ሆኖም ለዛሬ እሱን በመዝለል በሚቀጥለው ሰሞን እንደማቀርብላችሁ ቃል እየገባሁ፤ የዚያን ትችት ክፍለ ጊዜ አሁን የተቀራመተው ፋታ ያልሰጠኝ በቅርቡ “ሲያትል የተካሄደው “ፊረስት ታይም ኢትዮጵያንሰ ፎረም” (ባማርኛ ፈልጌ ስላጣሁ ርዐስሱን በሰየሙት ስም ተጠቅሜአለሁ) በሚል የተካሄደው ስብሰባ ውሸትና ስድብ ሲስተጋባ ዝም ማለት አላስቻለኝም እና እሱን ለዛሬ እንመለከት። ትችቱ ረዘም ስለሚል ከወዲሁ ትዕግስታችሁን እጠይቃለሁ።
በዚህ የመምህሬ የሟቹ የፕሮፌሰር ዓለሜ እሸቴን (ነብስ ይማር!) አባባል ለእነ ግንቦት 7ና መሰሎቹ ባዶነት መገለጪያ የመግቢያ ጥቅስ ልጥቀስ እና ይዤአችሁ ልግባ።
 
“For some time now this OLF stand has been supported by "well-intentioned" and "patriarchal gurus (with or without hidden agendas) calling for the unity of ETHIOPIAN OPPOSITION PARTIES to topple the Woyane. A rotten apple, plus a rotten apple, plus a rotten apple ---you may continue adding up - will never produce a good healthy apple” (Aleme Eshete (source –“Oromo NefTeNga- When The OLF Political sky Gets Darker. Response to Dr. Ghelawedos Araia. By Getachew Reda September 18, 2003) http://www.geocities.ws/oromosociety/Oromo_and_Nafthenya.html

ይህ ጉባኤ ከሌሎቹ ካሁን በፊት የተደጉ ኦነግና መሰሎቹ የጨመረ ስብሰባ ውሸትን በማስተጋባት የተለየ እንኳ ባይሆን ለየት ያደረገው ነገር ቢኖር “የኦሮሞ ጥያቄ አንድነት ሃይሎች ነን የሚሉ "ኦነግ ተገንጣይ ነው" እያ ለሕዝብ የዋሹት ውሸት እንጂ ኦነግ በውኑም በሕልሙም አልሞበትም፤ አስቦበትም፤ ጽፎትም፤ተናግሮበትም አያውቅም” የሚለውን አስበርጋጊ ደማቅ ውሸት እና እንዲሁም የግንቦት 7 ጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ የሆነው ፊልድ ማርሻል ጀኔራል ዶ/ር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ስያትል ስብሰባ አዳራሽ ባነነበበው የጽሑፍ መልዕክት፤ በመመርኮዝ እተቻለሁ።

ብርሃኑ ነጋ




ስለ አንድነት ድርጅቶች እንዲህ ሲል ያጣጥላቸዋል።
“በተግባር የሌሉ; "የቃላት" አንድነት ሃይሎች እያሉ ራሳቸውን የሚጠሩ ክፈሎች ቢሰድቡንም እኛ እንደ ግንቦት 7 መልስ ላለመስጠት በሰለጠነ ፖለቲካ ለመጓዝ ከወሰንን ቆይተናል የተቀራችሁትም ሆነ እነሱ በዚህ ስልታችን እንዲጓዙ ጥሪ እናቀርባለን ሲል ይቆይና ደቂቃ ሳይሞላው እኛን ኦባማን ከተሳደቡት ጽንፈኛ /አልትራ ወግ አጥባቂ/ እና ያበዱ ውሾች ከሚባሉት ነብሰ ገዳዮች ከጆን በርች ሶሳይቲ” ቡድኖች ጋር በማያያዝ የሰደብንን ስድብ ሳዳምጥ ነው  “ውሸታሞቹን ስንት ጊዜ  እግዚሐር ይማራችሁ እንበላቸው” በማለት ልተችበት የፈለግኩት።

ሰውየው በዚያው ስድብ አልተወሰነም።
"ባንድነት ስም የሚያቅራሩ መፈክር አሰሚዎች እና ፎካሪዎች ነብሳቸውን የምትዳስስ አስፈሪ ነገር አጠገባቸው ስትደርስ አገር ጥለው በመሄድ የመጨረሻዋ ጥይት አንጐነጫለን ያሏትን ሳይጐነጩ እየፈረጠጡ ወደ ውጭ የሄዱ ብዙ ናቸው። መንግሥቱን ጨምሮ!" በማለት አገር ጥሎ; ድምበር ተሻግሮ; ፈርጦ የመጣው ጋዜጠኛም ሆነ የፖለቲካ መሪ እና ያገር መሪ ሁሉ ፈርጣጮች ቸው:-  አገር ወዳዱ እና ቆራጡ ጀኔራል ብርሃኑ ነጋ ግን አገር ውስጥ ሆኖ እሱን ለመፈተሽ የመጣቺውን "ጥይት" አክሽፎ ፈርሃትን አንበርክኮ  "በረከት ስሞንን" ሳይማጠን አሁንም “ፍንፍኔ” ውስጥ "አካኪ ዘራፍ! የነጌ ልጅ! እያለ በመታገል እንዳለ በማስመሰል “ፈርጣጮች” ሲል የተመጻደቀበትን ስድብ ጨምሮ እንመለከት።
በኦነግ ልጀምር።
ኦነጐች እና ወያኔዎች ያጣላቸው መሰረታዊ ነገር እንደምታውቁት ኦነግ “የኦሮሞ ጥያቄ የኮሎኒ ጥያቄ ነው ያለ ቅድመ ኩነት መገንጠል እችላለሁ” ሲል ወያኔ እና ሻዕቢያ ያወጡት ባለ 66 ገጽ ማኒፌስቶ ደግሞ ‘የኦሮሞ ጥያቄ አንደ ማንኛውም የናሽናል/ብሔር ጥያቄ እስከ መገንጠል ድረስ ነው” በሚል ነው የተጨቃጨቁትና ወደ መተናነቅ የደረሱት። አሁን ኦነግ እነ ብርሃኑ ነጋን እየኰበኰበ ወያኔ የጋራ ጠላት ነውና አብረን እንምታ ሲለው; ብርሃኑ ተመልሶ የማይጨው ውርደታችን እየነገረን “ኦነግ የ100 ዓመቷ ቄሳራዊት ኢትዮጵያ ያስቆጣቺው ልጅ ስለሆነ “ናልኝ ሟሙሽ” እያላችሁ አስገቡት” ብሎናል። ሃብል ባንገቱ ያጠለቀ በሞቀ አልጋ የሚተኛ ክራባት አሳሪ ;በአዳራሽ “የአበባ ጉዝጓዝ” የለመደ ሽምቅ ተዋጊ አውሮጳና አሜሪካ ለመሸገ ነጻ አውጪ "የሟሙሽየ" "እፍ እፍ" ስልት ያታልለዋል ወይ አያታልለውም አብረን በሂደት እንመለከተዋለን።
 

አረጋዊ በርሔን/እና ሁለቱ የሻዕቢያ መንግሥት በVolunatry/በጐ ፈቃደኝነት ለሻዕቢያ ስራ አስፈጻሚነት  ደጀ ጠኚዎች  (ግንቦት7 እና ኦነግን) የጨመረ የስያትል ስብሰባ ከተካኼደ በኋላ “በኢትዮ-ሚዲያ” ድረገጽ ላይ ከስያትል ከአንድ “ግዕዝ ተናጋሪ” ኦነግ የተለፈፈው የውሸት ዕልልታ ጽሑፍ ጨምሮ ኢትዮ-ሚዲያ አዘጋጅ አብርሃ በላይ የለጠፈውና ያጋነነው ደማቅ ውሸት  እንዲሀም  እራሱ የኦነግ ጸሐፊ ነኝ የሚል “አሚን ጃንዳይ” ያስተላለፈውን ሃሰት ሁሉ እንመለክታለን።ወይ ትጉዱ! ይኼ ትግሬ ደግሞ ምን አመጣብን እንዳትሉ “የፊልድ መርሻሉ”ንግግርን ነው የማስደምጣችሁ። አትቸኩሉብኝ የፈጠራ አይደለም።
ኢትዮጵያን ላለመጥራት ተጠይፏት “ያቺ አገር” እያሌ አስሬ ሲጠራት ኢትዮጵያ አይደለሁም ወይንም ነኝ ለማለት እና ላለማለት ተቸግሮ ዳር ዳሩን ሲዞር የዘላበደውን የኦነጉን ፀሐፊ ንግግር እንጀምር። “የኦነግ አጀንዳ መገንጠልን ነው ብሎ ማሳነስ አይገባም።” “የኦሮሞ ሕዝብ ከትግሬው ከአማራው…እንደዚህ አይነት አገር (ኢትዮጵያ) የምትባል አገር እንመስርት ብሎ የተፈራረመበት ወቅት የለም።” 

እሰኪ እዩት ይህ ቅዠት ምን ይባላል? ኦነግ በዓለም ውስጥ ያልታየ አገራዊ ምስረታ “ፌርማ” የሚለው ከየት አንዳመጣው አይገርማችሁም። አሜሪካ እንግሊዝ ጣሊያን ሩሲያ ቻይና….ሀሉም እየተፋጀ እየተጋባ እየተገበያየ ነው አገር የመሰረተው በፌርማ እንዳልሆነ እየታወቀ።ኦነግ በዚህ በተመራመረ ዘመን “አገርን” የሚያክል የፈጣሪ ትልቅ አገራዊ ምስጢር እረስቶት ልክ እንደ ባልና ሚስት  “ በጋብቻ ፌርማ” አገር እንደማይቀና እና እንደማይመሳሰል  እየታወቀ  ኢትዮጵያ ስትመሰረት “የቤት ህንፃ” ይመስል ‘ፌርማ” ሚባል ነገር  አልነበረም; ካለ ደግሞ አሳዩን ሲለን “ኦነግ” በግብዝ መሪዎች የተሞላ ብቻ ሳይሆን ድርጅቱ ጭራሽኑ የባሰበት በሽተኛ መሆነን ተረዱልኝ።
ነገሩ “ግንጠላ” የምትለዋን ቃላት በዘዴ በማምለጥ ('ሰታብሊሽመትን' ተክቷታል) ሲሞክር ኦሮሞ ያለው ከቦታው “ኦሮሚያ ሪፑብሊክ” ውስጥ ነው፤ የተፈራረምንበት አገራዊ ምስረታ የለም: ስለዚህ ከማን ነው የምንገነጠለው በማለት በዘዴ ለመሸወድ ፈልጐ ነው። “የኦሮሞ (ህዝብ) ያለው በቄዬው ነው፤ ታዲያ (የኦሮሞ ህዘብ ) ማንን ወረረ? የማን አገር ወሰደ?” እንግዲህ ኦሮሞ ያለው ከቄየው ነው! ከማን ነው የሚገነጠለው?" ሲል አድማጮቹ ሳይገባቸው ይሁን አውቀውት ጭብጨባውን አቀለጡት።  ኦነግ ሲታመም አብረው የሚታመሙ ክፍሎች አሉ ማለት ነው። ቁንጪ ሓሚሙ ቁማል ተሓጒሙ (ትግርኛው) “ቁንጫ ታሞ ቅማል ዋግምት ገባ” (መሰለኝ ትርጉሙ)።
ልክ የነጋሶ ጊዳዳ ድርጅት አዲስ አበባ ውስጥ በቅርቡ ጋዜጠኞች “ስለ ግንጠላ አስመልከቶ ”በአንደነት ግምባር ውስጥ የተካተቱ የብሔር ድርጅቶች መገንጠልን ያካተቱ ወይንም በመገንጠልን እንደ መብት በፕሮራማቸው ያሰፈሩ  የሚያምኑ አሁንም ሉ ሲጠየቅ; በድርጅታችን ውስጥ “እስከ መገንጠል የሚያምኑ አሉ፤ ቢሆንም ‘ለማስገንጠል እንታገላለን” ከሚለው ይለያያል። አዎ ላለማለት በዘዴ ለመሸሽ ሲል የቃላት ጨዋታ ውስጥ እንደገባው ማለት ነው። የኦነጉ አማን ጀናዳይ ይሁን ነጋሶ ጊዳዳም ብቻ ሳይሆን  በቃላት ጨዋታ የሚሸውዱ ብርሃኑ ነጋ “ባላጋራ” “ጠላት” ምናምን እያሉ ቃላት ጨዋታ ውስጥ እንደሚገባው ዓይነት ማለት ነው። የዶከተር ጌታቸው በጋሻው እማ አይወራ “ኦነግ ነጻ ኦሮሚያን እመሠርታለሁ ሲል ሰምቼ አላውቅም” (see Allula አሉላ አባ ነጋ ፓል ቶክ ሩም http://www.abugidainfo.com/amharic/?p=6954 ),

ትዝ ይላችኋል የድሮው የዶክተር በየነ ጴጥሮስ የሕዝብ  ግንኙነት የዛሬው የግንቦቱ የሕዝብ ግንኙነት አቶ ኤፈሬም ማዴቦ የተባለው ሰው ስለ ኦሮሞ ነጻ አውጪ ትርጉም ሲነግረን? በኦሮሞ ነፃ አውጪ ግምባር  እና  የኦሮሞ ነፃነት ግምባር ልዩነት የማይገባቸው ደንቆሮዎች አሉ፡ብሎናል ኤፍሬም ማዴቦ የቃላት ስንጠቃ ውስጥ ሲገባ። እንደ እኔ የገረመው ወዳጄ አቶ ጊዜው ደረሰ “አዘለም አሉ አቀፈ ሁሉም ተሸከመ ነው” ብሎ የአማርኛውን አጠቃቀም ዘይቤ አስተማረው። ልክ አንዳርጋቸው ጽጌ የጻፈው ዘረኛው “የአማራ ሕዝብ ከየት ወዴት” ስለሚለው መጽሐፉ ተጠይቆ ዘረኛ መጽሐፍ መሆኑን ለመሸፋፈን ሲመክር “መጽሐፍም ነው ለማለት አይቻልም። ያው ትንሽ ገጽ ያላት መጽሐፍ ብጤ ነች….” ይላል። ሰዎቹ ጥፋታቸውን ላለማረም ይቅርታ ተሳስተናል ማለት ዳግቷቸው ላለማመን እንዴት እንዴት ዙርያ ጥምጥም ዳር ዳሩን እንደሚሸሹ ማየት ያሳዝናል።“አንተ ነጋዴ እያላችሁ ለምን ትሳደባለችሁ ገበያ ከደመቀ ምን ደኅና አለ።” መጽሐፈ ጨዋታ  ገጽ 20 (አሁንም ወዳጄ የላከልኝ ግሩም መጽሐፍ ካገኘሁት)::
ወደ አሚን ጃንዳይ ንግግር ልቀጥል
“ ስለዚህ የኦሮሞ ጥያቄ አሳንሶ ወደ መገንጠል ጥያቄ ለመውሰድ የሚፈልጉ ቡድኖች ወይንም ሕዝቦች የኦሮሞን ሕዝብ ችግር መፍትሔ ላለመስጠት የተደረገ መከራ/ዱለታ ነው እንጂ የኦሮሞ ነፃ አውጪ የኦሮሞ ሕዝብ  (ኦሮሚያ ሪፐብሊክ የሚባል አገር ለመመስረት እታገላለሁ ብሎ አያውቅም) ይገንጠል ብሎ አንድም ቀንም አልተናገረም የጻፉትም እስከነመረጃቸው መምጣት ይችላሉ።”
ይላል አሚን ጀንዳይ (የኦሮሞ ነፃ አውጪ ዋና ጸሐፊ/ “የኦሮሞ ነፃነት ግምባር” ብየ በአቶ ኤፍሬም ማዴቦ አጠራር ልጠቀም 'እንዳይቆጣ') ልብ በሉ። የኦነግ ጥያቄ የመገንጠል ጥያቄ መሆኑን ባንዴራው እያውለበለበ 40 ዓመት የዋሸውን ውሸት ግጥም አድርጐ ክዷል።ይህ አባባል ፖለቲካውን ያልገባቸው እና የኦነግ ውሸታም እና ዳር ዳር ሩጫ ባሕሪ ያላወቁ ሰዎች “መገንጠል ጠይቆ አያውቅም” ሲላችሁ ኦሮሞዎች የሚኖሩት በተፈጠሩበት ስታብሊሽድ በሆነው “ኦሮሚያ ሪፑብሊክ” በምትባለዋ ኦሮሞ የሚባል ሰው ሁሉ የትም ይኑር የትም በሚኖርበት አገርና ቦታ ሲፈጠር የኖረበት ስለሆነ ከየት ነው የምንገነጠለው እያለው ያለውን አበክራችሁ መመለከት ያስፈልጋል። ስለዚህ የምንገነጠለው ከየት ነው? የሚለው አባባሉ ይግባችሁ። የሚገነጣጠሉት በኦሮሞ መሬት /ድምበር “ዙርያ የከበቡትን ጎሳዎች  ባዲሲቷ ሪፑብሊክ ስፋት/ስታብሊሽመንት የሚጋረዱት ናቸው እንዳይገናኙ የሚጋረዱት/የሚገነጣጠሉት እንጂ  ትልቁ ሰፊው አሮሚያ አይደለም የሚገነጠለው/ የሚጋረደው ማለቱ ነው (ከሁሉም ጋር መገናኘት ይችላል ማለቱ ነው)። ይኼ በጣም ወንጀል ነው።
ሳይታወቀው ሸወድኩኝ ብሎ ያመለጠቺው አንዲት ሐረግ ቱክረቴን የሳበቺውን ግን ልግለጽ። እንዲህ ይላል “ስለዚህ የኦሮሞ ጥያቄ አሳንሶ ወደ መገንጠል ጥያቄ ለመወሰድ የሚፈልጉ በድኖች ወይንም ሕዝቦች የኦሮሞን ሕዝብ ችግር መፍትሔ ላለመስጠት የተደረገ መከራ/ዱለታ ነው። ይላል።”
“ናተንስያ ንሓመተን” (የራሷን ለአማቿ )“የማየን ወደ አባዬ” አድርጎ ተወቃሾቹ “እኛ" ተገንጣዩ ከግንጠላው አጀንዳ ከተገንጣይነት “ነፃ” ለማድረግ መሞከሩ አስገራሚ ይሁን እንጂ፡ የመገንጠል ጥያቄ በፖለቲካ ስነ አስተዳደር ችግር እንደ መፍትሄ ከተወሰደ የመጨረሻው “አተላ” መሆኑን ብዙ ዓመት ስንናገረው “ግንጠላ መፍትሄ አይሆንም”  ስንል ብዙ ሰዎች እኛኑን “ነፍጠኞች” እና “የነፍጠኛ  አመለካከት” ነው እያሉን ነበር (ተመጻዳቂው ኦነግ እራሱ ጨምሮ)። ዋናው የመገንጠል አቀንቃኙ  “አን ጀንዳይ” 
መገንጠልን ለኦሮሞ ሕዝብ እንደ መፍትሔ የሚያቀርቡ “የሚያሳንስ” “ትንንሽ ሰዎች የሚያነሱት “የወራዶች” ጥያቄ/አጀንዳ’ መሆኑን ይሄው አውቆም ሳይውቅም ብቻ ያንን አስረግጦ በማመን “ነፍጠኛ” ከመበል ነፃ አውጥቶናል:: “ወፊርካ እቶ” ይላል ትግሬ “ውለህ በሰላም ግባ” እንደ ማለት።
ተገንጣዮች አይደለንም! መገንጠል “የደደቦች አጀንዳ” ነው ብሎ ኦነግ አለ፤ ብንላችሁ አታምኑንም ነበር።ደግነቱ በራሱ ወንበር አዘጋጆች ድረገጽ ውስጥ መነገሩን በጀን። ያ እንዳለ ሆኖ፤ ሚስተር አማን ጃንዳይ ስለ ተናገረው “ኦሮሞ በቀዬው ውስጥ ነው እየኖረ ያለው ማንም ሰው/ጐሳ መሬት አልወረረም/ወርሮ አያውቅም” እና “ኦነግ የኦሮሞ ሕዝብ ይገንጠል ብሎ/ኦሮሚያ ሪፐብሊክ ለመመስረት እንድም አጀንዳ አቀንቅኖ አያውቅም” ያለውን ውሸት ስታሸት ከግማቱ ብርታት የተነሳ ሽቅብ ይላሃል። ትግሬዎች እንዲህ ዓይነት ደማቅ ውሸት ሲሰሙ ብቻ ሳይሆን እያወቀም ቢሆን ሆን ብሎ ሁኔታውን ለመመዝመዝ መስመሩን የሚያጣምም ውሸታሙን “ለኽባጥ” ይሉታል። ማለትም “አቋመ ቢስ/እዚህም እዛም የሚረግጥ ጦጣ” “በሁለት እግር ሁለት ዛፍ ባንዴ ለመውጣት የሚሞክር” ማለት ነው። ግልጽ ለማድረግ “ካብ ኪሒዱ ዝርታዕ አሚኑ ዝካታዕ” ማለት ነው። “ክዶ ከመረታት አምኖ የሚሟገትና የሚሸነፍ ሰው ክብር አለው” ማለት ነው።
ኦነግ በአጀንዳው ውስጥ የመገንጠልን ጥያቄ በፍጹም አንስቶ አያወቅም ብሎ ከሚናገር “ደማቅ ውሸታም” ይልቅ የመገንጠልን ጥያቄ አቅርበናል ነገር ግን አሁንም አቋማችን እንዳለ ነው ወይንም አሁን ትተናል ብለው የሚሟገቱኝን አቋማቸው ግልጽ ያደረጉ ኦነግያኖች አከብራለሁ። ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች ምን እንደሚፈልጉ ግልጽ ነው። ኦነግ የመገንጠል አጀንዳ አልነበረውም የለውም /አልጻፈም/  አልተናገረም/መዝገበን ፈትሾ  መገንጠል ነገር አይገኝበትም/ ልገንጠል ብሎ አልጻፈም…ወዘተ  የሚል የደመቀ ውሸት እና አራዳነት የሚያስተጋባ ግለሰብ  ግን በጣም አታላይ፤ ሆን ብሎ የታዳሚውና ያታዛቢውን ሕሊና ዝቅ አድርጎ በመመለክት አድማጮቹን “ሞኞች” ብሎ የሚሳለቅ ሰው ነው።
ካገር ቤት እየሸሹ ለብዙ ዘመናት የጫካ ህይወት በመጥላት እነኚህ የኦሮሞ ነፃ አውጪ መሪዎች ነን የሚሉን በኦሮሞ  ስም የሚነግዱ ቁጥር ስፍር የሌላቸው በአውሮጳ እና አሜሪካ የሚኖሩ "መሪዎች" በጣቶቻቸው ቀለበት ባንገታቸው ሃብል በትላልቅ አልማዝ እና ወርቅ አሸብርቀው ውድ የሆኑ መኪኖች እየነዱ እና ውድ በሆኑ ቤቶች እየኖሩ ህይታቸው የሚገፉ እነኚህ “የውሸት ሽምቅ ተዋጊዎች” (ቫኒላ ጉሬላ) ነው የሚባሉት? ካልተሳሳትኩ? ሳይሆን የሚገርሙኝ እነሱን ሚከተሉ አባሎቻቸውን በጣም አዝንላቸዋለ

ከወራት በፊት የአርሊነግተን ስብሰባ ውስጥ ብርሃኑ ነጋ እና አዲሱ “የኦነግ ጸናጽል” ደ/ር ጌታቸው በጋሻው ሆነው ስለ ኦነግ ማንነት ሲዋሹን፡ ዜግነቴ  ኦሮሞ ነው የሚል አንድ ወጣት “ዕድሜ ለኦነግ “ኦሮሞ ነኝ” ብየ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ቆሜ ደፍሬ እንድናገር ስላደረገኝ ኦነግ ምስጋና ይግባውና “ቅንጅት” አንድ ባሕል ፤አንድ ሃይማኖት፤ አንድ ቋንቋ፤አንድ አገር የሚለውን አጀንዳው አሁን ደግሞ ግንቦት 7 በፕሮግራሙ ሊደግመው ይሆን? ይህን በሚመለከት ምንድነው አቋማችሁ?” ብሎ ብርሃኑን የጠየቀው ትዝ አለኝ::

(የኦነግ አባሎች እንዴት በውሸት ቅስቀሳ እንደሚወናበዱ ለማሳየት ምሳሌ ልስጣችሁ ብየ ነው)።

ጠያቂው እንዲህ ብሎ ሲጠይቅ፡ ብርሃኑ ነጋ አንጀቴን ያኔ አራሰኝ (ከዚያ ሁለ የብርሃኑ ነጋ ሙጃና አራሙቻ የሞላው አቅማዳ ውሸቱ ማለቴ ነው)። ብርሃኑ ነጋ እንዲህ አለው፡ ‘አንተ በየትኛው የቅንጅት አጀንዳ ነው እንዲህ ዓይነት የተዛባ መረጃ ያገኘኸው? አንተ ነበርክ አዲስ አበባ? እኔ ነበርኩ አንተ አልነበርከም የኔ ወንድም! እንዲህ ብሎ ነገር አንድም ቅንጅት ፕሮግራመ ላይ አታገኘኘም። ቅንጅት በሌላው ነገር ማማት ትችል ይሆናል እንጂ “በስቱፒዲቲ” ልተከሰው አትችልም። አልተባለም። የት አንዳገኘኸው እና ማን እንደነገረህ ልትነግረኝ ትችላለህ? ብርሃኑ ነጋ ዝርዘር ፕሮግራሙ አጠር አድርጐ ሲጠቅስለት ...”  “ኦነግየው” ቆማ  ሳታስበው ጐርፍ የወሰዳት ጥጃ መስሎ “ሰመም” (ሲንሳፈፍ) ሲል አይቼው፡ - ያኔ ብርሃኑን እውነት “በመናገሩ አመሰገንኩት”።
እነኘጂ የመሳሰሉ የዋህ ተከታዮቻቸውን እየዋሹ ነው ኦነጎች እስከ ዛሬ 40 ዓመት የበሰበሱት። 

መሪዎቹ በጎረቤት አገር ኬኒያም ሆነ ኡጋንዳ አሜሪካም ሆነ አውሮጳ እየኖሩ ለምን ጫካ ይዛችሁን አትኼዱም ብለው ጠይቀዋቸው አያውቁም። ምክንያቱም ተከታዮቻቸውም ሙቀቱ ለምደውታልና ብርዱ ጥማቱ የኦሮሞ እረኛ የምስኪኑ ገበሬ ልጅ እንዲቀምስላቸው ስለሚፈልጉ እነሱም “ኦሮሚያ ኦሮሚያ ሪፑብሊክ” እያሉ ሃምበርገር እየገመጡ “ራፕ-ሚዩዚክ” እያደመጡ አብረው በውሸት ዓለም ተዘፍቀዋልና የሚገርም አይደለም። እውነቴን ነው የምነግራችሁ! ነፃ አውጪ አውሮጳ እና አሜሪካ አገር ውስጥ ምን ሥራ አለው?

እነኚህ የዋህ የኦነግ ከበሮ መቺዎች ብቻ ሳይሆኑ የአሚንን “ደማቃ ውሸት” በጭብጨባ ሲክቡ የነበሩት እነ አብርሃ በላይ (ኢትዮ ሚዲያ እና ስማቸው አሁን ለጊዜው ለመጥቀስ ያልፈለግኳቸው በይደር የያዝኳቸው የድሮ የወያኔ አባሎች) በድረገጹ ላይ የለጠፈው ደማቅ ውሸት እስኪ እንብቡትና ተወያዩበት እነሆ፦
“Amin Jundi: secessionism has never been the agenda of the Oromo people Ethiomedia | November 17, 2011” SEATTLE - Amin Jundi, Secretary of the Oromo Liberation Front (OLF), said reducing the quest of the Oromo people for democracy and justice to "secessionism" was unfair since "secessionism" has never been the agenda of the Oromo people nor of the OLF. Impressive in presenting his ideas both in Oromiffa and Amharic languages, the articulate Amin Jundi brightened the mood of the audience that has for a long time been forced to portray the OLF as a separatist group. Aregawi Berhe of UEDF and Berhanu Nega of Ginbot 7 also dwelt at length how to consolidate the opposition camp and move on to dislodging the tyrannical regime of Meles Zenawi.”
ልዘርዝረውና እንወያይ። አብርሃ በላይ- አሚን ጀንዳይ የዋሸውን ውሸት ምን ሲል እንዳደመቀለት እነሆ “, the articulate Amin Jundi brightened the mood of the audience that has for a long time been forced to portray the OLF as a separatist group.” እንግዲህ ኦነግ ሳይሆን እኛ ነን በአድማጩ ሕሊና ውስጥ “ኦነግ የመገንጠል አጀንዳ ያለው” ብለን “ያልዋለበትን ያላለመውን፤ያለ ስሙ እና ያለ ዓለማው በመስጠት” ዋሽተን ለብዙ ዓመታት  የኢትዮጵያ ሕዝብ አሳስተን  እንዲያምን በማድረግ ኦነግን  በአድማጭ ሕሊና ተገንጣይ ነው በማለት እንዲጠላ ያደረግነው ሲል እኛኑን ወንጅሎናል። ያውም (ሃዝ ቢን ፎርስድ) የምትለዋን ሀረግ ንከስዋትና “the audience that has for a long time been forced to portray the OLF as a separatist group”
 

አብርሃ በላይ የተቀበለው እና ያደመቀው ውሸት አሚን ያለውን በማድመቅ ብቻ ሳይሆን እሱም አምኖበት “ውንጀላው/accusation” አርቲለት” እንደሆነ ነው የገለጸው። ጃንዳይም እንዲህ ሲል ይወነጅለናል፡

“የኦሮሞ ጥያቄ ወደ መገንጠል ጥያቄ ለመወሰድ የሚፈልጉ በድኖች ወይንም ሕዝቦች የኦሮሞን ሕዝብ ችግር መፍትሔ ላለመስጠት የተደረገ መከራ/ዱለታ ነው እንጂ የኦሮሞ ነፃ አውጪ (ኦሮሚያው ሪፓብሊክ የሚባል አገር ለመመስረት እታገላለሀ ብሎ አያውቅም) ይገንጠል ብሎ አንድም ቀንም አልተናገረም የጻፉትም እስከነ መረጃቸው ማምጣት ይችላሉ።”
መዝገቡን ላቅርብ እነሆ፡
The Oromo Liberation Front (OLF) is a political organization established in 1973 by Oromo nationalists to lead the national liberation struggle of the Oromo people against the Abyssinian colonial rule.( OLF USA Office P.O.Box- 73247 Washington, DC 20056SA-USA-Phone #: (206) 462-5477 Ext. 202-Fax #: (202) 332-7011) አሁንም ተለጥፎ በፕሮገራሙ የሚነበበው ሕያው መመሪያው አንደሆነ ማረጋገጥ  ከድረ ገጹ ማረጋገጥ ትችላላችሁ።
አልቀየረም።
- Hence, the OLF political objective is liberation from Ethiopia and establishment of the Republic of Oromiya. (እንደ ላይኛው አሁንም 1974 እስከ ዛሬ የቀጠለው ፕሮግራም) http://www.oromoliberationfront.info/objectives.htm

-MAP OF OROMIYA REPUBLIC – shows-  MORE THAN HALF OF ETHIOPIAN TERRITORY EXTENDING TO ABAI IN THE NORTH AND HARAR IN THE EAST. Capital sity of Ormia Republic – Finfine (እንደ ላይኛው)።
እንግዲህ በዚህ ፕሮግራም ስትመለከቱ
The aim of the Oromo struggle led by the OLF is only to gain back our country that was taken away from us by force. It is not, in any way, against the rights of any other people. (OLF USA Office P.O.Box- 73247 Washington, DC 20056SA-USA-Phone #: (206) 462-5477 Ext. 202-Fax #: (202) 332-7011)

ይህ የሚለው የኦሮሞ  ነፃ አውጪ ድርጅት ፕሮግራም እና በድረ ገጹ ተለጥፎ ዛሬም የሚታይ ነው። ብዙ በኦነግ የሚጠሩ ኦ ኤል ኤፎች አሉ። ታዲያ ማንኛቸውን ኦነግ እንመን? ሁሉም በኦነግ ነው የሚጠሩት። መልከአ ምድሩ “ሪፑብሊክ ኦፈ ኦሮሚያ” ይላል “ስፋቱ ሦስት አራተኛ ያገሪቱ የቆዳ ስፋት በካርታው አስቀምጦታል” ታዲያ መጠሪያቸው “ኦ ኤል ኤፍ” (ኦነግ) ፕሮግራማቸው አንድ ሰንደቃላማቸው አንድ ጽሑፋቸው “ላቲን” እና “ሁሉም “ዜግነታችን ኦሮሚያ እንጂ ኢትዮጵያ አይደለም፤ለ ኢትዮጵያ ባዕድ ነን” ብለው ራሳቸው የሚገልጹ ከኣእላፍ ኦነጐች ማንን ለይተን “አይደለንም ሲሉን ኢትጵያዊያን ናቸሁ እንበል?”  (ናችሁ ካልን ደግሞ “ሰስድብ አለ፤ ኦሮሞ አንጂ ኢትጵያ አየደለሁም” ብሎ እስኪ በቃህ ይሰድብሃል።

ታዲያ እንዴት መገንጠልን፤ የኢትዮጵያ አንደነትና አገር ማፈራረስን አያቀነቅንም ማለት ይቻላል? የ ኦነጉ ጸሓፊ “አማን ጃንዳይ” ኦ ኤል ኤፍ አገር ለመገንጠል አልተነሳም አላለም ፤አልጻፈም ይላል። ፕሮግራሙ ግን ከላይ ያነባችሁት ነው። ታዲያ ከዚህ የባሰ የደመቀ ውሸት አለ? ይሄ ነው ደማቅ ውሸት የምላችሁ። ደማቅ ውሸት ደግነቱ እንደ ባውዛ (ሓዊ ለይቲ (በትግርኛ) አማርኛ “አጭበርባሪ ብርሃን” ልበለው) ደምቆ ይቆይና በጨለማ ዓይንን ያስደሰተ አጭበርባሪ መብራት በደቂቃዎች ራሱን በልቶ ከድቶህ ይጠፋል። ዓይንህ ተጭበርብሮ ጭለማ ውስጥ ተውጠህ ቁጭ!
 
እውነት እኛ ነን ሕዝቡን ኦነግ የመገንጠል አላማ አለው ብለው በፕሮግራሙ እንደ መመሪያው ያሰፈርንለት? አብርሃ በላይ “ፖርትረይ” ሲል ምን ማለቱ ነው። ያልሆነውን ሆነ ብለው ሚናገሩ መላት ነው። እኛ በገዛ አጀንዳው ውሸታሞች ሆነን ኦነግ አውነተኛ ሲባል፤ “ዘበን ያ ግርመቢጥስ ማይ ንዓቐብ” (!?) ግርምቢጠኛ ጊዜ ከላይ ወደ ታች መዝነቡን ትቶ ከታች ወደ ላይ ሲዘንብ ይህ ተገላቢጦሽ ዘመን ምን እንበለው?”

ፖለቲካ ለማሳመን አንዳንድ ቅመም መቀመም የታየ የተለመደ ብልሃት ነው። ነገር ግን ራስህ ፈስተህ ፈሳሽብኝ እሳ ምነው? ስትላት ለዚህ ውሸት ምን የሚባል ስም ይውጣለት? ለዚህ ነው ባለፈው ሰሞን ትችቴ ውስጥ ተቃዋሚ ነን የሚለት ድረገፃች አብዛኛዎቻቸው ወገንተኞች ብቻ ሳይሆኑ ውሸትን እያደመቁ ሕዝብን እያሳሳቱ ነው፡ ያልኩት ከላይ በኢትዮ ሚዲያ አብርሃ በላይ የተለጠፈው ውሸታሞችን “አርቲኩሌት” “አስተዋይ/ብልህ” እያለ ያለውን “የፖለቲካ ደላላነት” (ሎቢ) አስተውሉት ።  የኦነጉ “አሚን” ኦነግ ልገንጠል ብሎ በአጀንዳው ጽፎም ተናግሮም አያውቅም ብሎ ዑውር ውሸት ሲዋሽ ሰው ምን ይለኛል ብሎ “ትንሽ ሃፍረት’ አልተሰማውም። ምክንያቱም የውሸት በሸተኞች ሲዋሹ እየዋሹ እንደሆነ አይታወቃቸውም እና ልዩ የሕሊና ሕክምና ያስፈልጋቸዋል። የሰከረ ሰው “ሰክራሃል” ስትለው አንተነን ተመልሶ “ውሸታም አልሰከርኩም” እንደሚለህ ሁሉ ማለት እኮ ነው።ከውሸታሙ ይልቅ ውሸቱን የሚያደምቁለት በሁለተኛ ደረጃ የታመሙ አዳማቂ በሽተኞችን ስንት ጊዜ “ይማራችህ” እንበላቸው? “ወትሩ ሕሙም ክንደይ ጊዜ ይብጻሕ? “ለረዢም ዓመታት የታመመን በሽተኛ በደረስከው ቁጥር ስንቴ “ እግዚሔር ይማርህ” ማለት ይቻላል?” ይላል የትግሬ ሰው። እውነትም ስንት ጊዜ ይማራችሁ እንበላቸው?

የገረመኝ ነገር ደግሞ አማን ደረቱን ነፍቶ ኦነግ ሰው አልገደልም፤ ምንንም ህዝብ አልበደለም ይላል። በግድያ መሳተፉን  መረጃውን ይመልከቱ

"[ (http://en.wikipedia.org/wiki/Oromo_Liberation_Front#OLF_policies) ደግሞ ኦነግ ሽብርተኛ አይደለም ይላልThe Institute for Security Studies stated that, "Changes in target selection has led to the assessment that OLF transformed from a revolutionary movement into a terroristmovement."[56] . ."[ (http://en.wikipedia.org/wiki/Oromo_Liberation_Front#OLF_policies)


አሁን ወደ ብርሃኑ ነጋ እናምራ።
ብርሃኑ ራሱን በውሸት ሲያሞካሽና ሲክብ “ቢሰድቡንም አንሳደብም” ሲል ይቈይና በሰከንድ የተናገረውን ስልጡን ንግግሩን ጥሎ ወደ ፋራ ፖለቲካው ወደ “ሰድብ” ይገባል። እራሱ ፈርጥጦ እንዳልፈረጠጠ ሁሉ ሌላውን ፈሪ እና ፈርጣጭ ሲል ጭብጨባ ተለግሶለታል። መረጃው እንሆ።

“ራሳቸውን በቃላት “የአንድነት ሃይሎች” እያሉ ራሳቸውን የሚጠሩ ሃይሎች ድርጊታቸው የአንድነት ጠላትን ሚያጠናክር እንደሆነ ልንነግራቸው ይገባል። ግንቦት 7 ከማንኛቸውም ድርጅቶች ግምባር ቀደም “የተግባር ድርጅት” ነው ብየ በድፍረትና በሙሉ ልብ ለመናገር እችላለሁ (ሞቅ ያለ የተለመደው የበሽተኞቹ የጭብጨባ ሱስ ይደመጣል) ። ግንቦት 7 በአንድነት ጥያቄ ያለው ተግባር እና ተግባራዊ እንቅስቃሴ በ ግቡ ለመጠየቅ የሚሞክሩ ሃይሎች እዚህ አሜሪካን አገር “የፕረዚዳንት ኦባማን ዜግነት ከሚጠይቁ አክራሪ የፖለቲካ ሰዎች “የደበርዘር ሙቭመንት” ከሚሉት ጋር የሚያመሳስላቸው ነገር አለ።….
…አይገባውም ብለው ከሚንቁት ሕዝብ መሃል ጊዜያዊ ድጋፍ ለማግኘት ብቻ ሲባል የሚነሱ “ኦባማ”እንዳለው ‘የፖለቲከ ማስመሳያ ቀልድ ጊዜ ወይም “ፖለቲካል ሲሊሲዝም” ገላጮች ብቻ ነው። ከማንም ጸረ ወያኔ ከሆኑ ኢትዮጵያዊ ሃይሎች “ምንም ዓይነት ያመለካከት ልዩነት ይኑረን” ከነዚህ ሃይሎች ጋር “አላስፈላጊ እንካ ስላንትያ”ላለመግባት ድርጅታችን ከተቋቋመ ጀምሮ በተግባር እየፈጸመ ያለውን ውሳኔ አሁንም እያከበረ እንደ ሚቀጥል ይህም  ለወደፊቱ አስፈላጊ አወንታዊ የስነ ልቦናዊ ድባብ ስለሚፈጥር ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች የምር እንዲወስዱትና ከልብ እንዲተገብሩት በአጽንኦት እጠይቃለሁ። አመሰግናለሁ” ብርሃኑ ነጋ። Dr. Berhanu Nega's speech on Ginbot 7 and Ethiopian Unity  http://youtu.be/B8Ytx8e2cW4)
“ለመሆኑ የኢትዮጵያ ፍቅር በምን ይለካል? ስለ ኢትዮጵያ አንድነት መፈክር ከሚያወርዱት ውስጥ ስንቶቹ ናቸው የመጨረሻዋን ጥይት ተጐንጭተው ቃላቸው በተግባር ፈጽመው አለፉት? መንግሥቱን ጨምሮ! (ብርሃኑ ነጋ ከሲያትል ንግግሩ የተገኘ) ምንጩን ለማየት ዩ ቱብ ገብታችሁ (Dr. Berhanu Nega's speech on Ginbot 7 and Ethiopian Unity  http://youtu.be/B8Ytx8e2cW4) አድምጡ።

ለመሆኑ ግንቦት 7 መልስ ላለመስጠት በሰለጠነ ፖለቲካ ለመጓዝ ከወሰንን ቆይተናል የተቀራችሀትም ሆነ እነሱ በዚህ ስልታችን እንዲጓዙ ጥሪ እናቀርባለን ሲል ይቆይና ደቂቃ ሳይሞላው እኛን ከኦባማ ጽንፈኛ /አልትራ ወግ አጥባቂ እና ያበዱ ውሾች ከሚባሉት ነብሰ ገዳዮች ከጆን በርች ሶሳይቲ” ጋር በማያያዝ የሰደብንን ስድብ እሱ ከሚለው “ምንም ዓይነት ያመለካከት ልዩነት ይኑረን” ከነዚህ ሃይሎች ጋር “አላስፈላጊ እንካ ስላንትያ” ላለመግባት ድርጅታችን ከተቋቋመ ጀምሮ በተግባር እየፈጸመ ያለውን ውሳኔ አሁንም እያከበረ እንደ ሚቀጥል ይህም  ለወደፊቱ አስፈላጊ አወንታዊ የስነ ልቦናዊ ድባብ ስለሚፈጥር ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች የምር እንዲወስዱትና ከልብ እንዲተገብሩት በአጽንኦት እጠይቃለሁ።” ከሚለው ንግግሩ በምኑ ሊጣጣም ይችላል? ፈረንጅ ሲጨንቀው “ካን ሳም ዋን ሐልፕ!” ይላል። ወገኖቼ እንዲህ ዓይነት ዘለፋ እራሱን ከሚያመጻድቅ ግለሰብ ሲደመጥ ነውር የሚለው ሰው ታጣ? አሁን እሱን ብንሰድበው እኛ እንዴት ልንወቀስ እንችላለን? ልታስረዱኝ ትችላላችሁ? “ዛኣኽለን ጥሒነን በዓለ ማርያም ይብላ” (የሚበቃትን ፈጭታ በዓለ ማርያም ነው ይብቃኝ” ትላለች ይባላል። የሚበቃውን ሰድብ ተሳድቦ ‘ላለመሳደብ ቃል ገብተናል” ይላል። ወይ ትጉዱ!
ብርሃኑ እየለጠፈብን ያለው የስድብ ስም “ጃን/ጆን በርች ሶሳይቲ/ሙቭመነት” እኮ በጣም አክራሪ፤ ነብስ ግድያ ውስጥ የሚሳተፍ፤ አገሮች ውስጥ ጣልቃ እየገባ አንድነትን የሚያውክ “ስም የታጣለት እግዚሃር የተጣላው ቀኝ አክራሪ እንቅስቃሴ ቡድን ነው”። ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት ወዲህ በተለይ በቀዝቃዛው ጦርነት መባቻ ላይ የተመሰረተ የዘረኞች እንቅስቃሴ እና አፍሪካ ውስጥ ኰንጐ (ፓትሪስ ሉቡምበ ወቅት) አንጐላ፤ሞዛምቢክ …ኒካራጉዋ…. እና በመሳሰሉት “ሶሻሊዝም” መስረተዋል በሚባሉት አገሮች ወይንም የሶሻሊስት መርህ ይከተላል በሚባል አገር ጣልቃ በመግባት ወይንም ሶሻሊሰት አመለካከት አላቸው ብሎ የጠረጠራቸው ታዋቂ ግለሰብ/መሪ (ኬነዲ- ኦባማ) የመሳሰሉት ሰዎች መጥፎ ተግባርና ስም በመስጠት የታወቀ ነው።
 
ይህ የተጠቀሰው ቀኝ አክራሪ ድርጅቱ የኦባማን የማንነት ዘር የጠየቀበት ምክንያት እኮ ዘረኛ ቡድን መሆኑን ቢታወቅም “ኦባማ” ጥቁር በመሆኑ ወይንም አፍሪካዊ ደም ስላለበት ሳይሆን “ሶሻሊስት/ኮሚኒስት” ነው ብሎ ስለመደበው ነው። ሶሻሊዝም ከነ ስሙ ከሰማ “ከጥቁር ቆዳነት” በላይ ሶሻሊዝምን የጠላል። እና ጠለፋ ውስጥ ይገባል። ይህ ድርጅት በጣም አደገኛ ከመሆኑ የተነሳ 'ከብላክ ዋተር' የባሰ ቅጥረኛ ነብሰ ገዳይ መሆኑ አንዳንዶቹ ይናገራሉ። ድሮ ሲኣይ ኤ በገባበት አገር ድርጅቱ ግምባር ቀደም ሚና ተሳታፊነት ነበረው። “ኪሊንግ ሆፕ” የሚለው መጽሐፍ ስታነቡ ይህ ጽንፈኛ (አልተራ ኮንሰርቫቲቭ) ድርጅት የሰራው የወንጀል እንቅስቃሴ አጸያፊ ነው።  ታዲያ ብርሃኑ በዛው ድርጅት ስም ነው ያንድነት ሃይሉን ሲያትል ንግግሩ ውስጥ ሲዘልፍ የተደመጠው። እንዴት የዚህ ሰው “አታካራ ውስጥ  እንካ ስላንትያ” ውስጥ አንገባም እያለ እንዲህ አይነት ስም እየለጠፈ የምር ጥሪ ነው ተብሎ ሰው ሊያምነው ይችላል? ለመሆኑ አማካሪዎቹ ምን እየበሉ ኖሮው ነው ይህ ጽሑፍ ሲያዘጋጅ ዝም ብለው የለቀቁት? የነ አብርሃ በላይ “ፈረስት ኢትዮጵያን ፎረም” “ተናጋሪ አርቲኩሌቶች” ይኼንን ይመስላሉ። እንግዲህ የመጪዋን ኢት ጵያ “ጋዜጠኞቻችን፤ መሪዎቻችን” ምን እንደሚመስሉ ካሁኑኑ የምናይበት ምልከት የሰጠን አጋጣሚ ነው።

አስገራሚው ደግሞ የሚከተለውን ተመልከቱልኝ። ብርሃኑ ነጋ እንዲህ ይላል፦
“ለመሆኑ የኢትዮጵያ ፍቅር በምን ይለካል? ስለ ኢትዮጵያ አንድነት መፈክር ከሚያወርዱት ውስጥ ስንቶቹ ናቸው የመጨረሻዋን ጥይት ተጐንጭተው ቃላቸው በተግባር ፈጽመው አለፉት? መንግሥቱን ጨምሮ! “ ብርሃኑ ነጋ ከሲያትል ንግግሩ የተገኘ።

እግዚሔር ውለታውን ይክፈለው እና ቴክሳስ የሚኖር ጥሩ ወዳጄ ትናንት የማይገኙ መጽሐፍቶች በፖስታ ልኰልኝ “መጽሐፈ ጨዋታ፤መንፈሳዊ” የሚለው መጽሐፍ ስመለከት በገጽ 12 እንዲህ ይላል “ሥጋም ፍራቱን እጅግ አበዛው ከታረደ በኋላ ምን ያንቀጠቅጠዋል፤ምንስ ያንበደብደዋል?”ይላል። በግ/ፍየል ከታረደ በኋላ ስጋው ሲርገበገብ ሲንቀጠቀጥ አይታችኋል አይደል? ትርጉሙ ይግባችሁ።

ብርሃኑ ታዲያ እንኳን ታርዶ ገና ለገና “ኦመታለሁ፤ይይዙኛል” ብሎ ምንም ሳይነኩት ከእስር ሲለቁት እግሬ አውጪኝ ብሎ ሕዝቡን አጣብቂኝ አስገብቶ፤ያለ መሪ አስቀርቶ፤ ሜዳ ላይ ጥሎት፤ ፈርጥጦ ለትምህርት ወደ ውጭ አገር መጥቶ “ተራራ ላይ ውጥተህ ተፈላሰፍ በለውኛል” ብሎ መራራዋን ሞት እና ጥይት አንዳትቀድመው አገር ጥሎ ቀድሟት መውጣቱን ዘነግቶት “መንግሥቱን” ፈርጣጭ ብሎ ዓለም ሙሉ እያደመጠው በሌላ ሰው ሲሳለቅ ምን ዓይነት ደፋር ሰው እንደሆነ ይገርመኛል።   እንኳን ብርሃኑ ነጋ ባለ ጦር ባለ ታንክ፤ባለ ኮማንዶ ነብስ ጠባቂ ያለው መለስ ዜናዊ ሳይቀር “ፍርሐት” ወርሮት እንደ ነበር ጥቅምት 2003/ኦክቶበር 2010 ቮልዩም 11 ቁጥር/ናምበር 21 “ፍርሓት” የሚለው ዘ ሐበሻ ጋዜጣ ላይ በእውቁ ኢንቬስቲጌቲቭ ጋዜጠኛ ኢየሩሳሌም አርአያ የተጻፈውን ስታነብቡ ለካ “ፍርሃት” ክፉ ነው፡ የማይጐበኘው ሰው የለም ትላለህ። ፍርሐት የማይበግረው ሰው ግን የግንቦቱ ጠቅላይ ጦር አዛዥ እና አዋጊው ጀኔራል ብርሃኑ ነጋ ብቻ ናቸው።

ለመሆኑ ኰለኔሉ ሲፈረጥጡ እኮ እንደ ብርሃኑ “ተራራ ላይ ወጥተው የፍልስፍና ትምህርት ለመማር” እንኳ ባይሆን እሳቸውም የራሳቸው የሰጡት ምክንያት አለ። ለመፈርጠጣቸው ምክንያት፤ ፈረጠጥኩ አላሉም: “ካገሬ ለመሰሰድ ምክንያት ለጉብኘት ለአስቸኳይ የስራ ስብሰባ ኬኒያ መኼድ ስለነበረብኝ፤ እንደኼድኩኝ ተቀናቃኞቼ መፈንቅለ መንግሥት አደረጉብኝ። ኬኒያውያኖችም ከዱኝ፡ ስለዚህ ለጊዜው ዚምባበዌ አመራሁ።” ነው ያሉት። ሁልም ፈርጣጭ የየራሱ የራስ መጠምጠሚያ መሸፈኛ “ሻሽ/መንዲል” አለው። ከብዲ ይጹሮ! ብኽድኑ! ትላለች አንዲት ትግርኛ የምትሞከር ኢትዮጵያዊት አገር ወደዳድ ሲገርማት (ሆድ ይቻለው/ይሸከመው! ተከድኖ ይብሰል!) ማለቷ ነው።

ስለዚህ ኰለኔሉም ሞት ሳትቀድማቸው ቀድመዋት ሲፈረጥጡ “ፈረጠጥኩ” አላሉም። የሰጡት ምክንያት የራሳቸው ምክንያት ሲሰጡን ፤ የግንቦት 7ቱ የጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ እና ዶከተር ፕሮፌሰር ፈልድ ማርሻል ጀኔራል ብርሃኑ ነጋ ደግሞ የወያኔ “ዊፕ/ጅራፍ” ቀምሶ ስላማያውቅ ‘እስር ቤት ውስጥ ሌሎች ሲገረፉ” (ስዬ አበርሃን “የምን  እሪታ የምን ጅራፍ ነው የሚጮኸው ብሎ ደንግጦ መጠየቁን አስታውሱት መጽሐፉ ላይ) ሰምቶ ሞት ላለመጐንጨት ተደናግጦ ያላደረገውን ወንጀል “አዎ ፈጽሜአለሁ” ብሎ “ፈርሞ” ሲወጣ “ወያኔዎች ሰውን ሲገረፉ የሰማው የብርሃኑ “ቂጥ” በፍርሃት ተምበድብዶ ሲንቀጠቀጥ የወያኔዎቹ ጅራፍ “ጀኔራሉ” ቂጥ ላይ ከማረፏ በፊት ሲፈረጥጥም ለመፈርጠጡ የሰጠን ሽፋን  “ባይ ኤኒ ሚንስ -ከትግሉ ቀደም ብሎ መቀጠል ያለብኝ ኤክስቴንሽን ትምሕርት የመቀጠል እቅድ ስለነበረ መውጣት ነበረብኝ” አለን እንጂ “ፈረጠጥኩ እኮ አላለም። ማን ፈረጠጥኩ እንዳለ ብርሃኑ ነጋ ብቻውን መፈርጠጡን ይመን? ሞኝህን ፈልግ አለ ያማራ ሰው!

ታዲያ ብርሃኑ ነጋ ““ለመሆኑ የኢትዮጵያ ፍቅር በምን ይለካል? ብሎ ይጠይቅና “ስለ ኢትዮጵያ አንድነት መፈክር ከሚያወርዱት ውስጥ ስንቶቹ ናቸው የመጨረሻዋን ጥይት ተጐንጭተው ቃላቸው በተግባር ፈጽመው ያለፉት? መንግሥቱን ጨምሮ!” (በርሃኑ ነጋ)
እያለ እራሱ ከፈርጣጮቹ አንዱ ትልቁ ጉሬዛ ሆኖ እያለ ሌሎቹን “ፈርጣጮች” እያሉ ሲመጻደቅ እና ጥያቄ ሲያቀርብ “ምሕረት የውርድ” (ምሕረቱን ያውርድ) ከማለት ምን እንበል?

መንግሥቱ አስመራ መሄድ አይችሉም፤ ሽምቅ ተዋጊ ማሰማራትና መምራት አይፈቀድላቸውም። ብርሃኑ ግን አስመራ መሄድ ይችላል፤ ጫካ መሄድ ይችላል።ጫካ መሄዷን ግን አልወደዳትም። ምክንያቱም መራራዋን ጽዋ መጐንጨት ያልለመደች ፈርጣጭ ነብስ “ወያኔ ጐማ እግሩ” ጫካ ውስጥ “ጦሽ” ብሎ ድንገት ቢመጣበት “አድነኝ ብሎ የሚማጸነው ጓደኛው በረከት ስሞን” እንደ ማያገኘው ያውቃል እና ነው! ወይ እኚህ መንግሥቱ ፈርጣጭ ሁሉ የእንጨት ፈለጣ ተማሪ መለማመጃ አደረጋቸው። ወይ አለመታደል! ያረጀ ግንድ ምሳር ይበዛበታል፡ የሚባለው ለካ እንደዚህ ነው።

ባንድነት ሃይሎች ላይ የስድብ ውርጅብኝ ማውረዱ የብርሃኑ ስድብ የገዛ እናቴ ንግግር አስታወሰኝ። እቤታችን ውስጥ የጠላ ንግድ ስለሚጠመቅ፤ እናቴ ሲነሽጣት ለደምበኞቻችን አለፍ አለፍ ብላ “ምን የመሰለ አምቧሻ” ትጋግራለች። ታዲያ እኔ እና ወንድሞቼ እህቶች ክፉ አመል ነበረን። ከተጋገረው ትኩስ ዳቦ ሰው ፊት ቆርሳ ስትሰጠን “የተባረክን ልጆች” እንድንባል “ደህና ጠገቤአለሁ፤ ለእንግዶቹ ይሁን”እንላትና ሰዎቹ ያሳድጋችሁ! ብሩካን ልጆች! ብለው ምርቃን ከሰጡን በኋላ፡ እናቴ ወዲያ ወዲህ ስትል እኛ ዞር ብለን ሳታውቅ ተደብቀን ዳቦው ሰፌድ ውስጥ ከተደበቀበት ወደ ኩሽና/ማዕድ ቤት በመግባት በግምጃ/ነጠላ የተከደነውን ትልልቅ ዳቦ እየወጣን እየገባን “ቆርመም” እያደረግን እየገመጥን፤ ሙሉ የነበረው ዳቦ “አይጥ” የበላው ይመስል ተቆርምሞ  እናቴ ዳቦውን ለሰዎች ለማደል ስትከፍተው “ክብ ቅርጹ ጠፍቶ” ተቆርምሞ ስታገኘው “አንታ ታይ ወሪዱና? ዋይ! ናይ ሰብ አናፁ እውንዶ ይገጥመካ! ታይ ማዓቱ ደቀይ?! ( ወይ ጉድ! ምን ጉድ ነው! የሰው አይጥም ለካ አለ እባካች ? ትል እና ፤እኛ እንዳደረግነው ስለምታውቅ  እንደነቃችብን ለማሳወቅ ስትል እኛን እያየች “ቆርማሚ ጐጐ ከፉእ አመል” ትላለች። “ዳቦ መቆርመምን የሚመስል ለማስጣል የሚያዳግት ኩፉ ሱሰኛ አመል ከቶ የለም” ማለቷ ነው። ስለሆነም የነኚህ ፖለቲከኞች ውሸትና የአድማቂዎቻቸው አመል  ፈውስ ያለው አይመስልም። ስንት ጊዜ ይማራችሀ እንበላቸው?
አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ
www.ethiopiansemay.blogspot.com (Ethiopian Semay) getachre@aol.com






Monday, November 14, 2011

ሕሊና ቢስ ተቃዋሚዎች ሚዲያዎቻቸውና የሻዕቢያ ገበን

To see the page/font with a wider range, please press the key Ctrl and + sign. To view the page/font with a narrow range, please press the key CTRL and _ sign.ከታች የሚታየው የወያኔ ገበና ማህደር አዲሱ መጽሐፍ ለመግዛት $30.00 ዶላር ሲሆን የአምናውይድረስ ለጎጠኛው መምህር መጽሐፍ ደግሞ $25.00 ወይንም ሓይካማ የሚል የትግርኛ መጽሐፌ ደግሞ $15.00 ዶላር ብትልኩ መጽሐፎቹን ማግኘት ትችላላችሁ።

Getachew Reda P. O.Box 2219 San Jsoe, CA 95109  Phone (408) 561 4836 getachre@aol.com Phone (408) 561 4836

ሕሊና ቢስ ተቃዋሚዎች ሚዲያዎቻቸውና የሻዕቢያ ገበን

(ክፍል 1)

ጌታቸው ረዳ


ባለፈው ሰሞን  ጣሊያን አገር ውስጥ በስደት የሚኖር ዳግማዊ ይመር በተባለ ወጣት ኢትዮጵያዊ በጣሊያንኛ የተዘጋጀ የኢትዮጵያውያን ሕይወት በሚመለከት  ካገራቸው ሲሰደዱ ወደ ሱዳን በማምራት ከዚያም በደላሎች በኩል ገንዘብ በመክፈል ወደ አውሮጳ አገሮች ለመሻገር ወደ ሰሐራ ምድረበዳ ሲያቀኑ “በደዊን” በተባሉ የኤርትራ (ራሻይዳ/ሀረንዱዋ) እና የሊቢያ የግብጽ ምድረ በዳ ቅይጥ ዝርያዎች በባርነት ተሽጠው ለመግለጽ የሚያዳግት የሕይወት ፈተና ሴቶች እየተደፈሩ ወንዶች እየተገረፉና እየሞቱ ያለፉበት ሕይወት በባርነት ተይዘው ከነበሩ ዜጎቻችን ጋር ያዘጋጀው  ቃለ መጠይቅ አቅርቤላችሁ  የነበረውን ጉዳይ የታወሳል።
በሊቢያ ፖሊሶችም ሆነ በራሻይዳ/በደዊን ዘላኖች እና ባርያ ፈንጋይ ድርጅታዊ ቡድን በዜጐቻችን ሕሊና እና ሕይወት የደረሰው ለማመን የሚያስቸግር ግፍ ስንመለከት በሊቢያ ፖሊሶች ወይንም በበደዊን ዘላኖች ላይ የሰው ባሕሪነታቸውን  ስንገመግም እኛ በሰብአዊ እና በማሕበራዊ መተሳሰብ ባሕሪያችን ከእነሱ የተሻልን እየመስለን በኢሰብአዊ ድርጊታቸው እየተቆጣን ለዜጎቻችን ያዘንን ሰዎች አለን። ስለ እኛነታችን የጭካኔ ባሕሪ አለፍ ብሎ  በዜና በጋዜጠኞች የሚጻፉ ቁርጥራጭ ዘገባዎች እንጂ ሙሉ ታሪኩን የሚዘግብ ክፍል ስለሌለን በደዊኖች እና አረቦች እንዲሁም ሊቢያዎች በዜጎቻችን ያደረሱት ግፍ እየተመለከትን በነሱ  ላይ ስንቆጣ የእኛነታችን ጨካኝነት ግን አላወቅነውም። ስለሆነም የኛ ባርያ ፈንጋዮች እና ብልት ቆራጮች የሰው ልጅ ከነሕይወቱ ወደ ገደል ገፍትሮ መግደል፤ 12 ሺሕ፣ 30 ሺሕ አማርኛ ተናጋሪ ዜጎቻችን ከነ ልጆቻቸው ከነበሩበት ከተወለዱበት አካባቢ በጉልበት እተገፈተሩ እንዲባረሩ ሲደረግ የዜና ዘጋቢዎቻችን የሚያስተጋቡት እምብዛም ነው። ቢዘግቡትም ዘገባዊ ክትትል (ፎሎው አፕ) ስለማያደርጉ  ተደጋግሞ ሲፈጸም ልማዳዊ በማድረግ ቸል ብለው ወደ ቡድናዊ  የፖለቲካ ዜና ወይንም  በአዳዲስ የማይረባ ዜና ትኩረት ይጠመዳሉ።
ለምሳሌ ባለፈው ወር “ኢሳት” የተባለው ዋሺንገቶን ዲሲ መሰረቱ ያደረገ  እነ ክንፉ አሰፋ (ኢ ኤም ኤፍ ድረ ገጽ አዘጋጅ) እነ የግንቦት 7 እና የመሳሰሉት ዘረኞችና እነ ንአምን ዘለቀ የመሳሰሉ ለሻዕቢያ ተቆርቁረው ባደባባይ ከሻዕቢያ “ማሕበረ ኮም’ ጋር ትከሻ ለትከሻ ተያይዘው ያገራችንን ሰንደቃላማ እያውለበለቡ ለሻዕቢያ መጠቀሚያ ፕሮፓጋንዳ  የሚጮሁ ግለሰዎች የሚመሩት የስዕለ ድምፅ የዜና ማሰራጫን ስትመለከቱ ወገንተኛ  መሆኑን የምትታዘቡበት ሁለት ነገሮች በቅርቡ የተከሰቱትን ልጠቁም። በቅርቡ “ሶሴፕ”  የተባለ ለብዙ አመታት ለማንኛውም ሰው ሶማሊ ኢትዮጵያ  ኤርትራ ሱዳን… ጥቃት ሲፈጸምበት ቀድሞ በመጮህ ዜናውን ለተለያዩ  የዓለም ተቋማት እያሳወቀ ተወዳዳሪ የሌለው በጐ ስራ የሰራ የእስረኞች ተከራካሪ ተቋም ሲጮህለት የነበረው ፤ላለፉት 19 ዓመታት በወያኔ ወህኒ ቤት ያለ ፍትሕ በቂም በቀልነት ሲማቅቅ ቆይቶ ሰሞኑን የተፈታው አቶ አበራ የማነ አብ ከእስር ሲፈታ ኢትዮ ላዮን  አሲምባ እና ደብተራው የተባሉ ድረገጾች ዜናውን ሲዘግቡት


የሻዕቢያ አሽቃባጮች  ለሆኑት ለእነ ኦነግ፤ለግንቦት 7፤ ለኦጋዴን ነፃ አውጪ… የመሳሰሉት የፖለቲካ ማሰራጫ የሚያገለግሉ እንደ  እነ ኢትዮ ሚዲያ፤ ኢትዮፎረም (ክንፉ አሰፋ) አቡጊዳ እና የትግራይ ጠላቶች የሚያካሂዱት ኢካድ ፎረም (ካረንት አፈይርስ) የተባለ ድረገጽ ግን የአቶ አበራ መታሰር እና መፈታት ከጉዳይ ሳይቆጥሩ ትናንት የታሰረው ደበበ እሸቱ ከወራት በሗላ ከትናንት በፊት ለተፈታው የቅንጅት/ የአንድነት አመራር የሆነው ተዋናይ ደበበ እሸቱ ሲፈታ ግን ኢሳትም ሆነ ከላይ የተጠቀሱት የግንቦት 7 እና የተገንጣይ ቡድን መናኸርያ አውታሮች የሆኑት ድረ ገፆች አሸብርቀው ደስታቸውን በመግለጽ በማስተጋባት ላይ ናቸው። ሶሴፕ በዚህ በኩል “ መብት ለኛ በደል ለነሱ አያዋጣም በማለት ሕዳር 1/2004 ዓ.ም ያወጣው የቅሬታ መግለጫ ውስጥ ለነኛ ወገንተኞች ማለት በኢትዮኢያዊነት የሚነግዱ የሻዕቢያ እና የተገንጣይ መልከቶች የሆኑ ድረ ገፀችና ራዲዮኖች” ያስተላለፈውን የቅሬታ መግለጫ  በኢትዮ ላየን፤ በአሲምባ እና ደብተራው በመሳሰሉ ያንድነት የዜና አውታሮች የተለጠፈውን ያወጣውን የቅሬታ መግለጫ ይመልከቱ።
በሚቀጥለው ምዕራፍ 2 በሚቀጥለው ሰሞን ግንቦት 7 የተባለው ጽንፈኛ እና ዘረኛ ቡድን ከኢትዮጵ ጠላት ደመኛ ጠላት ከሆነው ሻዕብያ ጋር እየተሞዳመደ ያለው ስራ በጣም አሳፋሪ የባንዳነት ስራ እየፈጸመ ስለሆነ ሻዕቢያ በትግራይ ሕዝብ በጽኑ ተፈላጊ ወንጀለኛ እና ደመኛ መሆኑን የፈጸመቸው ግፎች ላንባቢዎቼ ሳቀርብ የግንቦት 7 ባንዳዎች የወገኖቻችንን ሬሳ እየተሻገሩ ከሻዕቢያ ጋር እየተሳሳቁ 






የሚፈጽመሙት ተልእኮ መወገዝ  አለባቸው።

የትግራይ ህዝብና የኢትዮዮጵያ ሕዝብ ሻዕቢያን በወንጀል ይጠይቀዋል። በጽኑ! ግንቦት 7 ተባለ ድርረጅት እና አብረውት የሚብጡ የትግራይ ተወላጅ ተቃዋሚዎች ካሉ ካሁኑኑ ሕዝባችን እንዲኮንናቸው በሚቀጥለው ሳምንት የሩዋንዳ ዘር ማጽዳት ስራ የሚመሳሰል ሕዝባችን ይ  የፈጸመው ሻእቢያ ገበና ዝርዝር ይቀርባል ተከታተሉት።
ለዛሬ የማተኩረው ግን አደገኛ የሆነው የነዚህ ያዲስ አበባዊነት እና በአብሮሽ ፤አብሮሽ ዱለታ ትውውቅ  ውጭ አገር በስደት መናኸርያ እንደ ዳመና እየተሰባሰበ  ያለው እየተጠራቀመ የመጣው አደገኛ የሆነ የሊሂቃን ቡድን ጥምረቱ ስታስተውሉት  ላንድነት የቆምን ነን ይበል እንጂ በግብር እያሳየን ያለው ትእይንት ያው የምናውቀው ካገር በመሸሽ በስደት እየኖረ ካሁን በፊት ለቅንጅትን መፍረስ እንደ ማፊያ አይነቱ ተንኰል በመጎንጎን የወያኔ ዕድሜ እንዲራዘም ምክንያት የሆነው የጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ጥምረት ጥርቅም የሆነው ክፍል ካለፈው ባሕሪው እና አፍራሽ ቡድናዊ ሚና ሳይመረምር ስሕተቱ  ዛሬም በአደገኛ “የአርቦሽነት” የፖለቲካ ሽረባ በመሸረብ አንድነታችን የማፍረስ ስራ ላይ መቃጣቱን ቀጥሎበታል።በትዕቢት እየቀጠለ በማይክሮፎን የሚለፍፈው ውሸት በማግስቱ እየተጋለጠበት ሳይጣጣም እምቢ ብሎት አንዴ ከጠባቦች አንዴ ከፈረንጆች አንዴ ከሻዕቢያ እዚህም እዚያም በመርገጥ የሚዘላብደው እርቃኑ የወጣ ፖለቲካ ለምንታዘበው ክፍሎች በእጅጉ ይገርማል።
ይህ ከቅንጅት መፍረስ ካዲስ አበባ እየተጠራቀመ ወደ ውጭ አገር እየተጠራራ ወደ ስደት  የመጣው አደገኛ ቡድን ታዋቂ ሰዎችን በቡድንተኝነት ስሜት ከብቦ በተለያዩ የሕሊና መሳቢያ እየተጠቀመ ጅሆ (ሆስተጅ) ሙርከኛ አድርጎ ገራ ገር ታዋቂ  ሰዎችን በስነ ኣኢምሮ ካቴና አስሮ ለጉራው መጠቀሚያ ሲገለገልባቸው ይታያል።በጣም የሚገርመው ደግሞ ታዋቂ የሚባሉት የድሮ ቅንጅት መሪዎች ቃላችንን አናጥፍም ብለው ሲፎክሩ ቆይተው ወላጆቻችን እና ዘመዶቻቸን የቀመሱት የፋሽስቶቹ የእሳት ጠበሳውና ሉጓሙ ሲጠብቅባቸው ሕዝቡን እየጣሉ ትምህርት እንማራለን ብለው ውጭ አገር  በመምጣት ወደ ተማሪ ዓለም ተለውጠው እንማራለን የሚሉትን “ትምህርት” ከመቀጠል ፈንታ ዛሬም የአደገኛውና  የከፋፋዩ ወገንተኛው ቡድን መገልገያ መሆናቸውን እየቀጠሉበት ነው።የሚያስቅ ሳይሆን አሳዛኝ ድክመት ነው። እነኚህ ታዋቂ የሚባሉት ግለሰዎች ለጊዜው በየስብሰባው እየጋበዙ የድግሳቸው ማጣፈጫ  ጨው እና ምጥሚጣ እያደረጉዋቸው እንደሆነ እየታዘብን ነው። ለወደፊቱ  ደግሞ እነ ስየ አብርሃ ሆኑ እነ ብርቱካን መዲቅሳ እና አንዲሁም አሜሪካኖች ተራራ ላይ ወጥተህ ተፈላሰፍ አንቀልብሃለን ስለ ገንዘብ አታስብ ብለውኛል ብሎ እያለን ያለው  በሻዕቢያ ኤርትራ ተራራ ላይ ወጥቶም ይሆን እዚህ አሜሪካ ዳገት ተራራ ላይ ወጥቶ የተሰጠው ትምህርታዊ ጥናት ያገባድድ አያገባድድ የምረቃውን ቀን ሳይነግረን ድምፅ ማጉያው ከንፈሩ ላይ ሰክቶ፤ በየቦታው የሆነ ያልሆነ የመንደር ወሬ እየለቃቀመ “የአነጐችን አንድ መሆን አሁን አሁን ገና አሁን ስብሰባ ከመግባቴ በፊት ‘ኢመይል’ ክፍቼ ሳነበው የተሰማኝ ደስታ ስመለከት ኦነጐች የመገንጠል ጥያቄ አቆሙ ደስ ይበላችሁ። ኦነጐችን እና ኦጋዴኖች ተገንጣዮች ናቸው የሚሉዋቹህ ዋሾች በመጪዋ ዲሞክራሲያዊት ገነታዊት ኢትዮጵያ ቦታ ስለማይኖራቸው የተበላ ኦቁብ  መሆናቸውን እወቁ …” በማለት የሚዘላብደው የግንቦት 7ቱ መሪው ብርሃኑ ነጋ እና መሰሎቹ በትምህርት ጥናታቸው ይዘንላችሁ መጣን እያሉን ያለውን ድምፅ  አንድ ወዳጄ የላከልኝ “ለልጅ ምክር፤ ለአባት መታሰቢያ የተበላ በሩይ ወልደስላሴ (ብላቴን ይመስሉኛል ማርጋቸው) መጽሐፍ ውስጥ ሳነብ በጸረ አንድነት ቡድኖች ላይ የከፈቱት የማጥላላት ዘመቻ እና የተገንጣይ ጓዶቻቸው እፍ እፍ ጊዜያዊ አርቦሽነት ስናደምጥ የሚደመጠው ድምጻቸው “ሲጮሁ እለቁ እለቁ ያሉ የሚመስሉ ጠጉራቸውም ለማየት የሚያስጠይፍ ወፎችን” ይመስላሉ። ብላቴን እንደሚሉት ““ከወፎችም ወገን ድምጣቸው ያማረ ጠጉራቸው የለሰለሰ ይገኛሉ። ሲጮሁ እለቁ እለቁ ያሉ የሚመስሉ ጠጉራቸውም ለማየት የሚያስጠይፍ ወፎችም አሉ” ይላሉ። እነኚህ በውጭ አገር የሚንቀሳቀሱት በተቃዋሚነት ባርቦሽነት ባዲስ አበባነት እየተሰባሰቡ የሚገኙት መርዛማ እና ጐሰኛ/ወገንተኛ የሊህቅ ስብስቦች” በምዕራባውያን አሰተማሪዎቻቸው የተሰጣቸውን የቤት ስራ ትምህርት ሳያገባድዱ እየተቻኮሉ “ዘው” እያሉ የሚለፈልፉት ውሸት ትዕግሰት እንዲኖረን የሚገፋፋ አይደለም።

ይህ ውጭ አገር በተቃዋሚነት እየቀጠለ ያለው ቡዱን የተጠናከረው በንግድ ጨዋታ የተካኑ ተንኰለኞች የተበተቡት ድር በመሆኑ ትግል ዓለም ልምድ ለሌላቸው ወጣት ዜጎች በቀላሉ ያርበኝነት የምስክር ወረቀት በገንዘብ እየገዙ እንዲጭበረበሩ አድርጓል። ሌላም ሌላም።

አንድ አስገራሚ ነገር ላንሳላችሁና ላጠቃልል። “ገለልተኛ” ብሎ ራሱን የሚጠራ ኢሳት የተባለው የዜና ማሰራጫ ስትመለከቱት ባለፈው ሳምንታት ደ/ር ግሬጐሪ ከተባሉት አሜሪካዊ የሰው ልጆች መብት ተከራካሪ አበበ ገላው በተባለው ወጣት ጋዜጠኛ የተካሄደው ቃለ መጠይቅ የታዘብኩት ነገር ቢኖር አዘጋጁ የጋምቤላዎች እና የኦጋዴኖችን እና 200 የሚያክሉ በ1997 ምርጫ በወያኔ ፖሊሶች የተገደሉ ሰላመዊ ተቃዋሚዎች ብቻ ወያኔ የፈጸማቸው የዘር ማጥፋት ወንጀል መሆኑን በእንግዳው በኩል እንዲረጋገጥ ደጋግሞ ሲጠይቅ ፤ ለ30 ዓመት (20 ዓመት ብቻ አይደለም) ሙሉ በወያኔዎች እና በሻዕቢያዎች እንዲሁም  በኦነጐች እና በኦጋዴን ነፃ አውጪዎች የተለያዩ የሃይማኖት ሽብርተኞች ያደረሱት በአማራው ሕብረተሰብ የደረሰውን የዘር ማጥፋት ጥቃት አንድም ቃል አንድም አረፍተ ነገር ከጥያቄው ውስጥ አላስገባም።
ጋዜጠኛው አበበ በለው ከ200ው የሰላመዊ ሰልፈኞች ግድያ እና ከጋምቤላው ጥቃት በላይ በአማራው ሕብረተሰብ ያውም እስከ ሁለት ዓመት በፊት ሳይቀር (በዚህ ኢትዮጵያን ሰማይ የተለጠፈው ጀርምን ራዲዮ ያስተላለፈው ዘገባ አሁንም እዚህ ተለጥፏል ያድምጡትActive Ethnic Cleansing in Ethiop http://youtu.be/aJDyueu2Kek  ) ትኩስ ተከታታይ ጥቃት እየደረሰበት እንደሆነ ወጣቱ ዘንገቶት ሳይሆን ኢሳት የተባለው የስዕለ ድምጽ ዜና ማስተላለፊያ ጣቢያ ጋር የግንቦት 7 መሪዎች የሚባሉት መሪዎች ከጣቢያው አካላዊ ብልቶች/ማሓውር ውስጥ አንዱ ስለሆነ፤ ይህ ግንቦት 7 የተባለው ጣቢያውን ከመሰረቱት የጣቢያው አንደኛው አባል (“ማሓውር” ብራንች ማለት ነው በትግርኛው) የመሰረተው ግንኙነት ከሻዕቢያ ጀምሮ እስከ ድርጊቱን ፈጽመዋል ከሚባሉ ወንጀለኞች (ኦነጐች እና ኦጋዴን ተገንጣዮች…) የሚዳራ ወዳጃቸው ስለሆነ አልፎም የነሱ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል እስከሚመስሉ ድረስ የሚቆሙላቸው ድርጅት በመሆኑ እነሱን ላለመስከፋት በአማራው ላይ በየአቅጣጫው በተከታታይ የተቀነባበረው እና ቀጣይ በአማራ ሕብረተሰብ ላይ ያነጣጠረው ጥቃት ጋዜጠኛው አበበ ገላው ለዶ/ር ግሬጐሪ አንዲት አረፍተ ነገር ሳያነሳለት ማለፉ እኔኑን ባያስገርመኝም አንባቢዎቼ ግን ቃለ መጠይቁን እንደገና ልብ ብላችሁ እንድታደምጡ እና የናንተ ትዝብት እንድትጨምሩበት እጠይቃለሁ።ከተሳሳትኩ እታረማለሁ።
ኢሳት ገለልተኛ ነኝ ይላል። እንዴት ሆኖ? በተወሰነ የፖለቲካ መሪ እና ድርጅቶች ላይ ዘመቻ ማካሄድ እንዴት ገለልተኛ ያሰኘዋል? ባለፈው ሰሞን በኢሳት ላይ እንግዳ ሆኖ የተላለፈ መደብ “ደ/ር ፈቃደ ሸዋ ቀና” የተባለ የግንቦት 7 አባል በኢንጂኔር ሃይሉ ሻውል ያፈሰሰው ዘለፋ ይታወሳል። የድሮው ኢትኦጵ መጽሄት/ጋዜጣ አርታኢ የዛሬው የአሳት ስዕለ ድምጽ አዘጋጅ ሲሳይ አገና የኦነጉ ዲማ ነገዎ እንግዳው ሆኖ ሲያነጋግረው “ኦነግ የኢትዮጵያ/የደረግ ሠራዊት እንዳይፈርስ ተከራክረናል” ብሎ እስካፍንጫው የገማ ውሸት ሲዋሸን እያዳመጠ መቶ አለቃ ሲሳይ አገና  እራሱ ወታደር መሆኑን እያወቀ “ኦነግ” የተባለ ተገንጣይ፤ጸረ ማራ እና ጸረ ኢትዮጵያ ቡድን “በፊት አውራሪነት”/ግምባር ቀደም ሆኖ ወታደሩ እንዲፈርስ ያደረገው ኦነግ  መሆኑን በሚገባ አንጀቱ እያወቀው  ዲማ በታሪክ ፊት ሲዋሽ ቸል ብሎ ሲያልፈው (የዘር ማጥፋቱን ጉድ ለወያኔ ብቻ ሲጣል የተደመጠው አስገራሚ የኦነግ የየለንበትም ክሕደት በዋዛ በቀላሉ  ነካ ነካ ተደርጎ እንዲያልፍ ያደረገውን ሳናነሳ ማለት ነው) እኔ በጣም ተገርሜአለሁ።

ሰሞኑንም የገረመኝ ደግሞ ኢያሱ በርሐ የተባለው ዘረኛ እና ትዕቢተኛ/ትምክሕተኛ በወያኔ ህንፍሽፍሽ ጊዜ የሚገደሉት ሰዎች “በደላላነት” የ“አ ሽ ዓ”መሪዎች ፎርማቶሪ ሆኖ በእንደርታ ተወላጅ ተዋጊ ሃይሎች የፈጸመው አሰቃቂ ገበና ተረስቶ ዛሬ “ኢሳት” የተዋጣለት አርቲስት እያለ ድሮ ሜዳ ጫካ ሆኖ ሲዘላብዳቸው የነበሩትን ጸረ ኢትዮጵያ ዘፈኖችን “በኢሳት”  ጣቢያ በመልቀቅ “ኢያሱ ተገደለ ወይስ ሞተ? ” እያሉ ሲያዘፍኑልን ያደመጠ ሕሊና ያለው ሰው ሳይገርመው አልቀረም። በጣም የገረመኝ ግን ሕንድ አገር ውስጥ የዜጋ ያለህ እያለ ኢየሩሳሌም አርአያ ከእናት አልባ በሽተኛ ህጻን ልጁን ታቅፎ የድረሱልኝ ጩኸት ሲጮህ ደንታ ያልሰጣቸው  የኢሳት ዋና ዋና ሰዎች  ለቅንብር እንዲመችላቸው ማቀናበሪያ ፕሮግራማቸው በማድረግ አርአያ ተስፋማርያም አገር ውስጥ እያለ የዘገባትን ጽሑፍ አስደምጠውናል። መቸም የነዚህ ግለሰዎች ወገንተኛነት፤ትዕቢት የማያውቅ አድማጭ እውነት ይመስለው ይሆናል። አሳት ውስጥ ያሉ ሰዎች ግን (ሁሉም አንኳ ባይሆኑ) እንደሚዘላብዱት ሳይሆን ለቡድናቸው ብቻ የሚጮሁ የሚደርሱ “ወገንተኞች” መሆናቸው ባለኝ ሰነድ በተጨባጭ መከራከር እችላለሁ ። አጫዋች  እና  ዘፋኝ ታማኝ በየነ ጌታቸው ረዳ ስለ አርአያ (እየሩሳሌም) አርዳታ ጉዳይ ምን ብሎ ተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርቦልህ ነበር ብላችሁ ጠይቁት። ምን እንደሚመልስላችሁ ከነገራችሁኝ በሗላ መረጃው እነግራችለሁ።  በትግርኛ አንዲህ ያለ ነገር ሲገጥም እንዲህ ይባላል “አድጊ አብ ምእራጋ መስከብ ትወልድ ዒሉ ሓዲጋ”  “ አህያ ልታረጅ ስትል ውርንጭላን መውለድ ትታ የእንግዴ ልጅ ትወልዳለች” ። እንግዲህ እንዲህ አይነት ኩራት የሚያሳዩት ለምን ይመስላችል? ሊሂቅና አርቦሽ አርቦሽነት ስብስብ ሲጎለብት ጉልበት ያለው/ኦምኒፖተንስ ስለሚመስለው ኩራታቸው መከራ ነው። አንድ ትግርኛ ምሳሌ ልጨምር “ አድጊስ ሳልሳይ ርእሳ እንተ ኾነት ዝብኢ ዝኽእላ ኣይመስላን” (አህያ ሦስት እራሷ ጋር ስትሆን ጅብ የሚችላት አይመስላትም”)
ኢሳት ግንቦት 7ን እያገለገለ ነው። ኢሳት እንደሚዘላብደው ገለልተኛ ሳይሆን ወገንተኛ መሆኑን አያጠያይቅም። አጫዋቹ እና ዘፋኙ (ኮመዲያን ይሉታል መሰል እንግሊዞች) ከላይ የጠቀስኩት ታማኝ በየነ የተባለው እንኳ ባለፈው “የኢሳት ዕርዳታ ማሰባሰቢያ ዕለት”  ባዘጋጀው መድረክ ላይ “ሰዎች ኢሳት  የግንቦት7 ነው ይላሉ፡ አይደለም! ቢሆንስ!” ሲል በጣም ኩራትና ልበ ደንዳናነት በተሞላበት ፈረንጆች “ጐ ቱ ሄል- ዘ ሄክ ዊዝ -ዩ! " ሦ-ዋት!” እንደሚሉት አይነት ድርቅና የተሞላበት ንግግር መናገሩ አድምጬዋለሁ። ሰውየው  ጥሩ ኢትዮጵያዊ መሆኑን  አልክደውም - ቢሆንም ትንሽ የሚጐድለው ነገር አለ። እሱ እና ብርቱካን መዲቅሳ በተንኰል በተካኑ ጋዜጠኞች እና ኤሊት ጋንጐች “ጁሆ” መሆናቸው ልብ አላለውም።  ሰውየው ለዚህ አባባሌ  አሳቂ  ችሎታው እራሱን ሊያስቀው ይችል ይሆናል፤እውነታው ግን አሱም እራሱ “ሂፕመታይዝድ” ያደረጉት ክፍሎች እንዳሉ አልተረዳውም እና ጊዜ ሲፈጅ ሲባንን ይረዳው ይሆናል የሚል እምነት አለኝ።
ኢሳት የግንቦት 7 ቢሆንስ ምን ልትሆኑ ነው! ማለቱ እጅግ አስገራሚ መልስ ነው። ግንቦት 7 ኢሳት የሚቆጣጠረው ከሆነ “  አይ ሃቭ ኤ ፕሮብሌም” ይላሉ ፈረንጆች “ባባሉ ችግር አለኝ”ማለት ነው። ግንቦት 7 አደገኛ አድር ባይ እና ውሸታም የሆነ ከሻዕቢያ ጋር የተቧደነ ፤ሻዕቢያ በሕዝባችን ላይ ያደረገው ግፍና የዘር ማጥፋት ወንጀል ግድ የሌላው፤ አሁን በየሳሕል እና በየጉራንጉሩ ዛፍ ተከላ እና ወረቅ ለቀማ ባሰማራቸው በባርነት የተያዙ አይናቸው የታወሩ ሻዕቢያ የትም የጣላቸው  ዜጎቻችን ቸል ብሎ ስቃያቸው ያልተሰማው ኢሳያስ ጋር ነጋ ጠባ እጅ የሚነሳው አንዳርጋቸው እና የብርሃኑ ድርጅት ደንታ ቢስ ካሃዲ መሆኑ ታማኝ በየነ ካላወቀው በሚቀጥለው ጽሑፌ የሊቢያ፤የሰሓራ በደዊን ባርያ ፈንጋይ አረመኔዎች ከሰሩት ወንጀል ያልተናነሰ ያውም የከፋ ዘገባ በተጨባጭ ከሰለባዎቹ የተገኙ በትግርኛ የተደረጉ የቃል ምልለሶች ባማርኛ ተርጉሜ  ዘግቤ  አቀርብላችለሁ። ታማኝም እንዲያነበው እና “ቢሆንስ! ምን ልትሆኑ ነው” ከሚለው ድርቅና ያድነው ዘንድ እንዲያነበው እዚህ ጋር እጋብዘዋለሁ። ለቅምሻ እነሆ  በክፍል ሁለት በሚቀጥለው ሰሞን ይለጠፋል።

ታሪኩ የተገኘው በቅርቡ “ጥልመት’ ከተባለ በወያኔው  በዶክተር ሰለሞን ዕንቋይ የተጻፈ የተገኘ ጥናት እና ታሪክ ነው።
“ቄስ ተኽለ አረጋይ የተባሉ የትግራይ ሠው የኤርትራ ወጣት ተማሪዎች በኢትዮጵያውያን በተለይ በትገሬ ሰዎች ላይ በሻዕቢያ ቅስቀሳ ተነሳስተው  የፈጸሙት ዘር የማጽዳት ዘመቻ እንዲህ ይገልጹታል… ይላል መጽሐፉ


““ቄስ ተኽለ አረጋይ የተባሉ የትግራይ ሠው ከረን ውስጥ ሲኖሩ ባረንቱ በኢትዮጵያ (በባድሜ ጦርነት ወቅት) ሠራዊት እጅ ከወደቀች በላ ወጣቶቹ በማግስቱ የወሰዱት እርምጃ እንዲህ ያስታውሱታል “ባረንቱ ውስጥ ባላስረጋ በተባለ ቦታ ተሰብስበው የነበሩ ወጣት ተማሪዎች ‘ዛሬስ የሚገደል ሰው አጣን፡ ሁሉም አጥርተናቸዋል መሰል። እነኚህ አጋሜዎች ሁሉንም ፈጅተናቸዋል መሰለኝ  የሚገደል አጋሜ በከተማው ውስጥ ብንፈልግ ልናገኝ አልቻልንም! ሲሉ ሰማቸው። ያኔ እኔኑን ያስፈራኝ ጉዳይ እነሱን መስየ/ኤርትራዊ መስየ ነበር የምዘዋወረው እና ደንገት እንዳይነቁብኝ ተጠራጠርኩና በውስጤ በጣም ሰጋሁ።
በወቅቱ አንድ የትግራይ ሰው የሆኑ ቄስ ወዳጄ አጥቻቸው እሳቸውን ፍለጋ ስዘዋወር ነበር የህ አስፈሪ የግድያ ዘመቻ ሲነጋገሩ ያደመጥኩት። ቄሱን ስፈልግ በድንገት ከአንድ የቆሻሻ መጣያ ቦታ አንድ ሬሳ ተጥሎ አየሁ። ህ ሬሳ ምንድ ነው? ብየ ስጠይቃቸው ‘የአንድ አማራ ሬሳ ነው” አሉኝ።

ሌላ ሦስት ሬሳ ደግሞ ጉል (ጉልዒ) ዛፍ ስር ወድቆ ተመለከትኩኝ። ከነዚህ ሬሳዎች አንደኛው ይኼ የምታዩት ከወደ እዚህ በኩል ያለው ሬሳ ‘አደንዝዝ” እየተባለ በፈረስ ስም  ስንጠራው የነበረው አጋሜው እኮ ነው እየተባባሉ ሰማቸው።…” 

በጣም ዘግናኝ የሆኑ የሻዕቢያ እና ጀሌዎቹ ዘግናኝ ገበና በክፍል ሁለት በሚቀጥለው ሰሞን ይቀጥላል። እነ ታማኝ በየነ ኢሳት የግንቦት 7 “ቢሆንስ!” እያሉ በድርቅና የሚደነፉት ዕብጠት ባንዳው የግንቦት 7 ድርጅት ከጌቶቹ ከሻዕቢያዎቹ ጋር ሲሞዳመድ ወገኖቻችንን የወደቀበት እሬሳ እየረገጠ አዛዣቸው ኢሳያስ አፈወርቂን ለመማጸን በደም መሬት ላይ እየተረማመደ መሆኑን መታወቅ አለበት። ይቀጥላል…።
አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ Ethiopiansemay.blogspot.com ( just Goole it Ethiopian Semay) getachre@aol.com