Sunday, May 25, 2014

ተቃዋሚዎች እና ሰንደቃላማችን

Note from the Editor;-
Dear Ladies and Gentlemen
I have a feed back that the font on my blog is too small to read for the eye. Here is the solution, what you can do if it is too small to read. On your keyboard, press 'Ctrl' key and hold it while holding that button press the + sign to magnify it. Or to downsize it- you can press the same key Ctrl and hold it and press the -sign situated before the - sign key. You can do this to all website pages.

ተቃዋሚዎች እና ሰንደቃላማችን

ጌታቸው ረዳ (የ Ethiopian Semay አዘጋጅ)

                                             ግንቦት 13/2006 ዓ.ም (May 21/2014)
አስቀድሜ አንዳስታወቅኩት፤ ከእንግዲህ ወዲህ የኔን ትችት ለማንበብ የምትፈልጉ በተቃዋሚዎች ድረገጽ ሳይሆን በእኔው ድረገጽ Ethiopian Semay ወይንም ፌስ ቡክ ብቻ አንደምታገኙኝ በድጋሚ አሳስባለሁ። የተቃዋሚ ድረገጽ አዘጋጆች ለሕዝቡ ይጠቅማል ለትግሉ አስፈላጊ ትችት ነው ብለው የሚያምኑትን ትችት በፈቃዳቸው ከድረገጼ ወስደው ከለጠፉት በስተቀር ካሁን ወዲህ በነሱ ድረገጽ ላይ አታገኙኝም።

የተቃዋሚው ችግር ብዙ ነው። አንዳንድ መሪዎች በፍርሃት የተሸበቡ ናቸው። አንዳንዶቹ ደግሞ አድርባዮች ናቸው። አንዳንዶቹም ግራ የተጋቡ ናቸው። በጠቅላላ ተቃዋሚው ስምረተ ሕልውናው በምን ላይ የተመረኰዘ አንደሆነ አያውቀውም። በትግራይ ባንቱስታኖቹ ግምባር ቀደም የተካሄደው ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ የኢትዮጵያ ስም እና ዝና ማጉደፍ፤ የከተሞችን ስያሜ መለወጥ እንዲሁም ሰንደቃላማዋን በሕዝቧ ፊት ማጣጣል፤ እና ሕዝቡ በራሱ ማንነት ላይ አንዲዘምት በውጭ ጠላቶች ለዘመናት የተሞከረው የጥቃት ዘመቻ፤ በአሳሳቢ መልኩ በተቃዋሚውም ክፍል ሴራው እውን እየሆነ ወረርሽኙ እያጠቃቸው በግዝገዛ ዘመቻው ላይ እየተካፈሉ ናቸው።

አምና ‘ድምጻችን ይሰማ’ የሚለው በጂሃዳዊው ‘በግራኝ አህመድ’ “አሞጋሾች” የተሞላበት እስላማዊ እንቅሰቃሴ የጀመሩት የተለያዩ ቀለም ያሉባቸው መንዲሎች (ጨርቆች) በውስጣዊ እይታው የግራኝ አህምድ የተሰበጣጠሩ የቀለም ጨርቅ አርማዎች የሚያንጸባርቁ፤ ራስን ከብሔራዊ ሰንደቅ የነጠለ ስሜትን ያቀፈ የኢትዮጵያ አገራዊ ሰንደቃላማን የሚያጣጥል እርምጃ ከታየ ጀምሮ እነሱን ተከትሎለው የመጡት “በዩዲጀ” የሚታወቀው በራስ ስም በቅንጅት አባልነቱ መቀሌ ድረስ በመሄድ ‘የትግራይን ሕዝብ’ ቅንጅት ውስጥ ባልተደረገ እና ባልተፈጸመ የዘረኝነት ይቅርታ የጠየቀው በአድርባዩ በኢንጂነር ግዛቸው ሺፈራው የሚመራው፤ እና እንዲሁም ወደ መድረኩ አዲስ ሆኖ በወጣቶች ስብስብ የሚጠራው “ሰማያዊ ፓርቲ” ተብሎ በሚጠራው በይልቃል ጌትነት የሚመራው ተቃዋሚ፤ የወያኔን ስርዓት ለመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በጠሩበት ጊዜያቶች ሁሉ ለክብራቸው እና ለማንነታቸው የሚያውለበልቡት መለያ የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ ሳይሆን፤-የተለያዩ ቀለም የተቀቡ መንዲሎች/መሃረሞች/ጨርቆችን በማውለብለብ ነበር።

Our men with their yellow rag avoiding the Ethiopian flag

ይህ ባሕሪ የተቀዳው ኦራንጅ አብዮት፤ ቀይ አብዮት፤ሰማያዊ አብዮት ወዘተ ወዘተ በመባል የሚጠራው የቀድሞ የሶቭየት ግዛቶች የነበሩት ዛሬ ለቀውስ የተዳረጉ ትንንሽ “አገሮች” በሚያውለበልቧቸው የተለያዩ  ቀለሞች የያዙ ጨርቆች የተቀዳ ባሕሪ ነው። አረቦች እና እስላም አገሮች በዚህ በኩል ሰንደቃላማዎቻቸውን በማንገብ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችን አስንቀዋል።
UDJ and its white, red, yellow flags insinuating the Ethiopian flag in Addis Abeba protest

UDJ  building hoisting different colors of flags

Semayawi Party with its unknown circled code on its blue flag




በኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ከሚመራው “መ ኢ አ ድ” በስተቀር የተቀሩት ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጡ የአገራችን የማንነት ኩራት እና መለያ የሆነቺው ሰንደቃላማችንን በማስወገድ ላይ የተሞረኮዘ ነው። ይህ እርምጃ ከጣሊያን ጀምሮ የተጠነሰሰ ሴራ ዛሬ በዚህ ዘመን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በተቃዋሚውም በኩል እውን እየሆነ ለሴራው ተባባሪዎች ምቹ ሆነዋል። ስለሆነም አዲሱ ትውልድ የሚመካበትን ብሔራዊ ማንነት እያሳጡት ነው። ለጥቃቱ ግዝገዛ ሁሉም መጥረቢያቸውን ይዘው በመገዝገዝ ላይ ይገኛሉ ስንል፤ አዲሱ ትውልድ የኔ ነው የሚለው ብሔራዊ ማንነት በዛ ተከትሎ የሚታገልለት እሴት በዝግታ፤ቀስ በቀስ  እንዳያውቅ እየተደረገ ስለሆነ፤ የቅኝ ግዛት ወረርሺኝ ጥቃቶች ለመከላከል ‘ተረካቢው ትውልድ’ በራሱ ላይ እየተጐነጐነ ያለውን “ሴራ” እንዲያውቀው ያለመሰልቸት ለ22 ዓመታት እየጮህኩኝ ያለሁትበት ምክንያት ይህ ሴራ እውን እንዳይሆን ነው። ጥቂቶች ናቸው በሚል ማጃጃያ ሴራው እንድንንቀው እያደረጉ በዝግታ የተነሳው ሴራ፤ ዛሬ ባለንበት ሂደት የት ላይ እንደደረስን ባፈሩ/ግስገሳው በሩን ለመስበር የት ላይ ቆሞ እንዳለ መመለክቱ የሚከብድ አይመስለኝም።

MEAD protesting with its proud Ethiopian flag protesting in Sawula town few weeks a go

አስገራሚው የግዝገዛው ሴራ እና ተባባሪነት ሰንደቃላማችንን በማስወገድ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ፤ በሴራ ጠንሳሾች የታቀደው ኢሕጋዊ እና ተሪካዊ አልባ በሆነ መልክ የአገራችን፤የከተማችን፤ስሞችን በመቀየር ሁሉ ተባባሪዎች ሆነዋል።

ከወያኔ እና ከኦነግ ሚዲያዎች እየተቀበሉ ተቃዋሚ ነን የሚሉት የፖለቲካ ድርጅቶች እና ውጭ እና ውስጥ አገር ያሉ ሚዲያዎች ሁሉ (ኢሳት የስም ለውጥ አስተጋቢ ዋናው የግዝገዛው ተባባሪ ነው። ዘሃበሻ የተባለው ድረገጽ የኢትዮጵያን ኢሕጋዊ የሆነ የወያኔ የአገራችን መልክአ ምድር የለወጠ ካርታን በመለጠፍ፤ የግዝገዛው ሴራ መሪ ተዋናይ እና አስተዋዋቂ ሆኗል። እና የመሳሰሉ የተቃዋሚ ሚዲያዎች…..) አዲስ አበባን “በፍንፍኔ” ፤ ናዝሬትን “ በአዳማ” ወዘተ ወዘተ… የመሳሰሉ የስም ለውጦች ተባባሪነታቸው እያሳዩ ነው።

ፋሺስቱ እና ቅጥረኛው የወያነ ትግራይ ቡድንም ሆነ ቡቹላው የኦነግ ቡድን የሴራው ጠንሳሾች ናቸውና ከነዚህ ከቅጥረኞች የሚጠበቅ ባሕሪ ነው። ሆኖም የቅጥረኞቹ ሴራ ተባባሪ የሆኑት የተቃዋሚ ድርጅቶች እና ሚዲያዎች ግን የሴራው አዳማቂ ሆነው ሕዝቡ ይህንን ሕገ ወጥ የሆነ  ‘ወረርሺኝ እና ጥቃት” እንዲቀበለው የበኩላቸውን ግዝግዛ እያደረጉ ነው። ይህ የአናርኪዎች እና የአጥቂዎቻችን ስብከት እና ሴራ ተባባሪነታቸው እያሳዩ ሕዝባችን ማንነቱን እና ዳር ድምበሩን አንዲክድ እና አንዲጠራጠር በማድረጉ ዘመቻ ላይ አስተዋጽኦ እያደረጉ ናቸው።

ተቃዋሚው እና የታወቁ የህግ ባለሞያዎች እና የፖለቲካ ተንታኞች የሚባሉት ኢትዮጵያዊያን የአገራችን ችግር የሃይማኖት አክራሪነት አይደለም፤ የፖቲካ ተገንጣዮች ችግር አይደለም፤ ችግሩ “የዲሞክራሲ እጦት ነው” እያሉ ነባራዊውን እውነታ ሕዝቡ እንዳያየው በዲሞክራሲ ሕልም አንዲዘፈቅ በማጃጃል ላይ ናቸው። ቀደም ብየ በቃለ መጠይቄ በግልጽ አንዳስቀመጥኩት http://youtu.be/pXtJPLbbL48 ዲሞክራሲ የአንድ አገር ሁለንተናዊ መፍቻ ሊሆን አይችልም። ዲሞክራሲ ሲሰፍን፤ ኗሪ አይደለም። አገር ግን ኗሪ ነው እና በዲሞክራሲ ተመርኩዞ ሊፈርስና ሊጠብ አይገባም። ተገንጣዩም ቢሆን በዲሞክራሲ የተስፋ አንጀራ ተመርኩዞ ከዋናው አገር ቢነጠል፤ የተነገረው ተስፋ እውን ሊሆን አይችልም። ዲመክራሲ በማንም አድሃሪ ወይንም በታጠቀ ወታደር በማንኛውም ጊዜ የሚነጠቅ ዋስትና የሌለው የአስተዳዳር ሂደት ነው። ዲሞክራሲ ለፍትሕ አስፈላጊ ቢሆንም፤ ዲሞክራሲም የፍትሕ እና የሰውነት መብት (በተለይ ብዙሃን በአናሳው ላይ) ተጻራሪ የሚሆንበት ጊዜ አለ። ገፋ ሲልም፤ ዲሞክራሲ “ናዚዎችን፤ጨቋኞችን” በሕዝብ ጫንቃ ላይ እንዲወጡም የሚያግዝ “ነፃ የሕዝብ ጋሪ ” የሚሆንብት ወቅት እንዳለ እና እንደታየም ልብ ማለት ተገቢ ነው።

 ይህም ማለት ወሮበላዎችን ፤ነብሰገዳዮችን፤አክራሪዎችን እና  ሰላማዊውንም አሳፍሮ ባንድነት አጭቆ የሚጓዝ ሉጓም የሌለው ‘ልቅ ጋሪ’ ነው። ዲሞክራሲ ግምብ ያልተበጀለት፤የሚጠለፍ፤ በሕልም የሚጓዝ ሰው ሰራሽ ሞለጭላጫ ‘አርት’ ነው። ዲሞክራሲ በማንኛውም ጊዜ እና ሰዓት በጉልበተኛ አንደምትጠለፍ ውብ ሴት ማለት ነው። ስለዚህም ሴረኞች እና ተቃዋሚዎች ‘ዲሞክራሲ’ ከአገር አንድነት ጋር እያዘማዱ እሱ እና እሱ ብቻ እንደ ፈውስ አድርገው በማቅረብ ሰፊ የማጃጃል ስራዎች እያካሄዱብን ነው።

ዲሞክራሲ ገደቡ የት ላይ ነው? በዲሞክራሲ መብት አገርን በመስገንጠል? አክራሪዎች በስፋት እንዲራቡ በመርዳት? የት ላይ ነው የዲሞክራሲ በሩ እና ድምበሩ? ተቃወሚውም ሆነ የፖለቲካ ተንታኞች ጊዜያቸውን የሚያተኩረበት “ዲሞክራሲ” አጥር አልባ ነው። ወያኔ ሲወገድ የሚከተለው “የተቃዋሚዎች ዲሞክራሲ” አንድ ሕዝብ እገነጠላለሁ ካለ በጠምንጃ አንይዘውም፤ በሕዝብ ድምፅ መገንጠል ይችላል፡ ብለውናል (ውጭ አገር የሚገኙት የዋሆችን ኩፉኛ በማጃጃል ላይ የሚገኘው የግንቦት 7 መሪ ከሁለት አመታት በፊት በኢሳት የሰጠው ቃለ መጠይቅ ልብ ይለዋል። ውስጥ አገር  ያሉትም አንደዚሁ ከዛው የተለዩ አይደሉም።ለግንጠላ ዓላማ እንዲያመች የተቀናጀው “ራስን በራስ ማስተዳዳር” የሚባለው ‘ዲሞክራሲም’፤ ሞገደኛ እና ጨቋኝ እስከወዲያኛው የሚያስወግድ ተምስሎ የሚሰበከው ይህ ‘ለየዋሆች የተዘጋጀው አደንዛዥ እጽ’ ላይ ላዩን ከመዳሰስ በቀር በጥልቀት ከአገር አፍራሾች ከወያኔ እና ከኦነግ “ራስን በራስ አስተዳዳር’ አጀንዳ በምን መልኩ አንደሚለዩ ያብራሩት ነገር የለም።)፤  የተቃዋሚዎች ዲሞክራሲ አገርን በማፍረስ ላይ የሚያነጣጥር፤ አዲስ አበባን ወደ ፍንፍኔ ፤ ናዝሬትን ወደ ‘አዳማ’፤ ኢትዮጵያን ወደ “ብሔር ብሐየረሰቦች” ስያሜ የሚለውጡ ከሆኑ ከወያኔዎች በምን ራዕይ ነው የሚለዩት? ከእናት ከአባቶቻችን የፍስሐ ስሜት እና አንድነት የሚነጥለን ዲሞክራሲ የሚያመጡልን ከሆኑ ‘ዲሞክራሲ’ ጥንቱም የሕልም እንጀራ የሆነ በኢምፔሪያሊስቶች የተቀየሰ “ሞለጭላጫ አርት” ነውና በር ተበጅቶለት ሕዝቡ እንዲገለገልበት ካልተደረገ ‘ዲሞክራሲ’ ለባሕር ማዶ ባለቤቶቹ ተሰጥቶ፤ ነባሩ ባሕላችን ጉዱፉን ከመልካሙ ለይተን መልካሙን አዳብረን በመጓዝ ለ22 አመት አገር እንደ አገር ማስኖር ያቃተው ‘ሰነፉ ዲሞክራሲ’ ይልቅ አንደ መንግሥት እና እንደ አገር ሦስት ሺሕ አመት ከጠላት ጠብቆ ያስኖረንን ‘አገር በቀል’ ጠንካራ ባህላችንን ለመምረጥ እንገደዳለን።

የአውሮጳ ጸሐፊዎች፤ጣሊያኖች ታሪካችንን አጣመው ጽፈዋል። ሰንደቃላማችን የጉራቸው መጠን ልካቸውን ስላሳየቻቸው፤ በጠላትነት አይተዋታል። አማራው ለአገሪቱ ሕልውና ከፍተኛ መስዋእትነት ከፍሏል። ሰንደቃላማችን እንድትውብለበለብ እየተራበ፤በድርቅ እየተገረፈ፤በውስጥ  እና በውጭ ጠላቶች ተከብቦ ከነነብሱ ወደ ገደል እየተገፈተረ፤ እየተሰደበ እና በመርዝ እየተገደለም ቢሆን ከፍ አድርጎ ይዟታል። ይህ በማድረጉ ጠላቶች ከጣሊያኖች ጀምሮ “አማራን ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያንን እና ሰንደቃላማችንን” አንድ አድርጎ በመሳል፤ በሦስቱም ላይ ጠላት በማደራጀት አንዲዘመትባቸው ተደርጓል። ጠላቶቻችን ይኼው ተባባሪዎች አግኝተው ፍሬው እያየው ነው። ስለሆነም ነው በነዚህ “ተቋማት እና ዜጎች” ላይ ጠላት ዓይኑን በመጣል፤ ከስር እንዲሸረሸሩ ያደረገው።

በጠላት ወገን የተሰነዘረው በነዚህ ተቋማት ላይ ሴራው ከባድ ቢሆንም የተነበየው እና የተፈለገውን የሩዋንዳ እና የማንሮቪያ ዓይነት እልቂት ወዲያውኑ ባለመታየቱ ዛሬም ቢሆን ሴራው እውን እንዲሆን ከመጣር አልቦዘኑም።  ሕዝቡ “የኔ” የሚላቸውን ተቋማት፤አርማዎች እና ስሞችን እንዲጠላቸው፤ቸል አንዲላቸውና አንዲያስወግዳቸው የተለያዩ አዘናጊ ስዕሎች በዜጎች ሕሊና ላይ በመሳል በየሚዲያው እያሰራጩ ነው።

አንድ ምሳሌ ልግለጽ፦

ሲያትል የሚኖረው ወዳጄ ደራሲው አቶ አማረ አፈለ ቢሻው “የሁለት ሺህ ዓመታት ውጣ ውረድ በኢትዮጵያ’ በሚለው መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይላል።

“ አንድ አርሶ አደር ሙክት ሊሸጥ ገበያ ሲሄድ ሽፍቶች አገኙት። ነገር ግን ሊቀሙት አልፈለጉም። ምክንያቱም  ደህና ጠንካራ ወንድም ስላለው ከገቡበት ገብቶ እንደሚቀማቸው ያውቃሉ። በሃይል ሳይሆን እውነቱን ‘ውሸት’ ብለው ራሱን እንዲጠራጠር ለማድረግ ተስማሙ።

ሽፍቶቹ ቁጥራቸው ወደ አስር ሲሆን አንድ በአንድ እየሆኑ ሰውየውን እንዲያገኙት ተስማሙ። ቃላቸው አንድ  ዓይነት ነው። በመጀመሪያ ያገኘው ሰው ሰላም እንደምን አደርክ ይለዋል። አርሶ አደሩም “እግዚአብሔር ይመስገን ደህና” ብሎ ሲመልስለት የት እየሄድክ ነው? ይለዋል። አርሶ አደሩም ይህንን ሙክት ልሸጥ ይለዋል። ሽፍታው የምትጐትተተው ‘ውሻ’ እንጂ መቼ ‘ሙክት’ ነው? ብሎት ይሄዳል።

ቆየት ብሎ እንዲሁ አንዱ ይመጣና ይህኑ ይለዋል። ከዚያም ሦስተኛ በዚሁ መልክ ከመለሰለት በሗላ ሁለት ሁነው ሲመጡ አንደኛው ለአንደኛው ውሻው እንዳይበላህ ተጠንቀቅ ብሎ ሲነግረው አርሶ አደር ይሰማል። ከዚህ በሗላ እርሱም እራሱን ተጠራጥሮ ሙክቱን ለቆ ወደ  ቤቱ ሲሄድ ሽፍቶች አርደው በሉበት። ይህም ሰው ያሳደገውን ሙክት ተጠራጠረ፤ ውሻ ነው ሲሉት ተወላቸው። እኛም ዛሬ የገጠመን ችግር የእኛን ታሪክ የእናንት አይደለም እያሉን ነው። ያንተ አይደለም ሲሉት “ለካ አውነት ነው” እያለ በመጠራጠር የሚቀበላቸው እራሱን የሚጠራጠር ብዙ የዋህ ሰው እያፈሩልን ነው።….. ስለዚህም ሴራውን ማክሸፍ ይጠበቅብናል።”

ኢትዮጵያን የሚያጠፏት አንደ ጠላት የመደብናቸው ‘ጣላቶቻችን’ ሳይሆኑ በጥቃቱ ግዝገዛ ላይ የጠላቶች ተባባሪዎች ናቸው ኢትዮጵያን የሚያጠፏት። ኢትዮጵያ የሚባል ስም ሲነሳ የሚበረግጉ “ተሸናፊዎች” የማንነቷን መገለጫ የሆነው ሰንደቃላማዋን ከዓለም እይታ እና ከዜጎቿ ዓይን እንዲሰወር፤ የክፍለሃገሮችን ሰፋፊ ለም መሬቶችን ወደ ትግራይ እንዲካተቱ፤ የከተሞቻችን እና ርዕሰከተማዋን ስም ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ አንዲለወጥ፤ ሲደረግ፤ አንዳንድ የዜና አውታሮች፤ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ተባባሪነታቸው በጉልህ እየነገሩን ነው።እነኚህ ክፍሎች ከሴረኞቹ ጥቃት በግዝገዛው ሴራ ለይ ከተባበሩ፤ የእናት ኢትዮጵያን መቀነት ከሚቀዳድዱ ወና ጠላቶች ለይተን ስለማናያቸው ከታቀፉበት ከሞቃቸው ደረቷ ላይ እባብ ሆነው ከመንደፍ አንዲታቀቡ ዛሬም መልእክቴ እንዲደርሳቸው ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።

የሚቀጥለው ትችቴ የሚያተኩረው ሆን ተብሎ ወንጀል ፈጻሚዎች በዩቱብ የተለጠፉ ሕዝብን የፈጁባቸው ወይንም የተሳደቡባቸው ማህደሮች ወደ ዩ ቱብ ባለቤቶች አቤት በማለት እንዲነሱ እየተደረገ ስለሆነ፤ ይህ ወንጀላቸው እንዳይታወቅ የሚያደርጉት ሴራ ለዩቱብ ባለቤቶች አምቢታ ማስሰማት እንዲለምደን የሚያሳስብ ትችት አቀርባለሁ። ይህንንም ሆን ተብሎ ፈሪዎቹ አቤት ሲሉ የዩቱብ ባለቤቶች ““This video has been removed as a violation  of You Tubes policy on shocking and disgusting content.” በሚል  ያስነሱታል። ዩ ቱብ ይህ ፍርደገምድል በኢትዮጵያ ላይ ብቻ እንጂ ‘በአሜሪካኖች፤ በኢራቅ፤ ባፍጋኒስታን፤ በታሊባን፤ በሊቢያ፤ባሰውዲ….ወዘተ…ወዘተ… አገሮች የሚለጠፉ ዘግናኝ ወንጀሎች ግን አሁንም ተለጥፈው ለዓለም ይታያሉ። ኢትዮጵያዊያኖች ለምን ልዩ ፍርድ ተሰጠ ተብሎ የዩቱብ አስተዳዳሪዎች መጠየቅ አለብን። ወንጀለኞቹ ምንም አንኳ ስዕለ ድምፁ ከዩ ቱብ እንዲነሳ ቢያደርጉም “ድምፁ” ስለቀዳነው ወንጀላቸውን መደበቅ አይቻላቸውም። ሆኖም የወንጀለኞቹ ማህደር በዩቱብ አንዲታይ የለጠፉት ተቃዋሚዎች ከሆኑ ለምን አንዲነሳ እንደተደረገ ፈቃደኞች እና ተባባሪዎች እንደሆኑ ለኔ ግራ የገባ ነገር ነው። በዚህ ላይ በሚቀጥለው እንነጋገራለን። አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ ካሊፎርኒያ አሜሪካ የEthiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ። getachre@aol.com


The Ginbot 7 Criminal Leaders



x- Hizbawi Hayl fighter  an Ethiopian Shitaw Shiferaw Victim of Ginbot 7 explaining how Ginbot 7 passed him to  EPLF to tortured him
The Ginbot 7 Criminal Leaders
By Getachew Reda (May 14, 2014)
I have argued for many years that the opposition is taken away by foreign mercenaries and criminals who are seen by their ignorant followers as their shining light on the hill that can do no wrong!
I am sick of the criminals leading the opposition in the Diaspora as I am similarly sick with the TPLF criminals inside Ethiopia.

Many understand me why I am frustrated by these Diaspora opposition,  and many fools also opposed me and asked me why I am frustrated by the so called opposition and their naïve “activists” and their destructive media. I have been on the front line for the last 22 years with my few friends, while the present thousands/perhaps millions of opposition hatched like  a turtle egg all over the Diaspora are late comers to the struggle. I am well familiar who is who, including the crooked elites who are hard to detect when they play political gambling.  

Heart breaking Tears!!!!!! Agony!!!!    - Victim of Andargachew Tisge Ginbot 7 fighter in Eritrea explain his ordeal of torture in Tears.
Though, I tried over and over explained to them in my written commentaries and interviews, why I am opposing them and fade up of their connive character, crime and their destructive activity against the political struggle and against humanity, many ignorant and their premature Diaspora opposition cults who are not better mature than the ordinary street gang bangers still failed to understand their leaders' psychopath and connive nature.

Their followers seemed to ignore the human dilemma as long as anyone try to remove TPLF. It could be criminal, monster, evil, secessionist, mercenary, it does not matter to these premature cults as long as any of their evil, monster, Nazi, connive. Psychopath individuals or organization remove TPLF from power.   You can hear these lunatic and lost cults heralding such scary view all over the anarchic Pal Talk rooms.

 Next week until I present you “how the opposition in Ethiopia such as UDJ, Semayawi, the Islamic movement/DimTsachin Yisema are avoiding Ethiopian flag replacing it by yellow, red, black, blue, or  white rag when they staged public protest.”  Until then, for today, I will present the crime of Ginbot 7 inside Eritrea headed by none other than the two psychopath leaders of Ginbot 7 Dr.Berhanu Negga and Andargachew Tsige. You need a strong heart to listen to the audio video presented by their victim. If you have soft heart, you will be easily broke in to tears with the victim  broke to tears.

So I advise you to be strong and finish the interview all the way. It is heart breaking when Ethiopians repeatedly given to Eritrean cruel torturers by Dr. Berhanu Negga and Andaragchew Tsige, who are simply thugs playing the life of our people worst than our enemy TPLF and EPLF. These psychopath criminals need to be sued in the international court for abusing humanity. That will not happen, because there are many activists individuals  like TamanG Beyene, and ETSAT journalists and the rest of the Diaspora sold-out elites and their puppet media hiding their crime by manipulating the mind of the premature Diapsora population as "Freedom Fighters". You can see the promotion on Zehabesha website or on Ginbot 7 own media ETSAT by the laughable puppy of Ginbot 7 member Dr Taddesse presenting his stupidity reading his thuggish master's book "NeTsanet Ye Mayawuk NeTsa Awchee". What mockery BLASH elite this fellow is!
We have seen TamNg Beyene crying wolf for humanity in public condemning TPLF’s crime, we have not seen yet, TamaNg Beyene as an Ethiopian activist crying and exposing or confronting or even mentioning an iota of word about the crime of his friends Dr.Berhanu Negga and Andargachhew Tsige.  How bias can one be than this open pick and chose defense of humanity? This guy is been talking about Humanity ever since 1991, you mean to tell me , he can't understand the tears and agony of the Ginbot 7 victims'?!
  
 I urge all my followers and readers, to spread this commentary on your face book all over the planet, since these Diaspora opposition media are embedded with those torturers and psychopath elites. They are hand and glove in this crime. TPLF will never be removed from power soon as long as these connive criminals are allowed to exploit and abuse our people. They are the tools of distraction supported by foreign enemies. The false picture given by the lunatic elites in the opposition that TPLF is breaking down and reaching at its 12 hour is a mockery to fool you. It can/t be, because, the opposition is romanticizing such myth  to itself without any strong spine of its own. TPLF was never strong, what made TPLF strong is the opposition who bent down in front of a hard ship in prison. They are still in such cocoon.

These criminals in Ginbot 7 as leaders of such crime are responsible for many wrongs since TPLF got into power.  Their present crime is documented on  video. It  is attached under this commentary for you to see the inner side of these political criminals who Andargachew and Berhanu Tsige looks like.

Many do not understand what torture mean, unless one is tortured by someone or perhaps “Unless one has been subjected to torture oneself, it is impossible to get an accurate sense of what it must be like to be subjected to it, which is why one can dismiss out of hand the excuses given by torture apologists that it is little more than fraternity hazing, although that is bad enough.”  Mano Singham.

Yes, torture is evil and those who committed it, provided the authorization for it, and gave the orders for it should all be prosecuted.

Please listen this audio video how Ginbot 7 member by the name “Shitaw Shiferaw” in Eritrea was tortured by Eritreans without eating a food for 12 long hour every day for months and months. He was been handed to SHAABIA by the anti Ethiopia, a monster and evil Andargachew Tsige.(leader of Ginbot 7 in Eritrea). This is why I was bitterly opposing Ginbot 7 and advised the Diaspora fools about Ginbot 7 leaders since the breaking of Kinijit. This fellow was tortured in the form of “WOFE LALA” what they called it in Eritrea “HELICOPTER”. The audio video interview is posted on Ginbot 7 Democratic (the group ridiculed and exposed he crime nature of the Ginbot 7 leaders), it reads like this...
“የህዝባዊ ሃይል ተብየው የአስተዳደርና ፋይናን ሃላፊ ከነበርው ሽታው ሽፈራው በህዝባዊ ሃይሉ ስም የሚሰበሰበው ገንዘብ እንደ አስተዳደርና ፋይናንስ ሃላፊነቴ ማወቅና አባላትም ግልጽ በሆነ አሰራር ማሳወቅ አለበን ብሎ በመጠየቁ ብቻ ሰበብ ተፈለጎለት በነ አንዳርጋቸው ትዕዛዝ እንዲታሰርና ለሻዕቢያ አሳልፎ እንዲሰጥ ከተደረገ በኋላ የደረሰበትን ግፍና በደል፤ ድብደባ በአጠቃላይ ከባርነት በከፋ ሁኔታ እንዴት እንዳሳለፈ ይህም እሱ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ኢትዮጵያውያን በሻዕቢያ እጅ እንዴት እንደሚሰቃዩና እንደሚገደሉም ጭምር ይገልጽልናል። ከሽታው ሽፈራው ጋር የተደረገ ውይይት ቪድዮ ከዚህ ቀጥሎ ይዘን ቀርበናል ሙሉውን በቀጣይ በተከታታይ ይዘን እንቀባለን”  http://www.ginbot7d.org/

I ask the Diaspora opposition, challenging them why going to Ethiopia to accuse another criminal when there are similar criminals inside the Diaspora opposition who are not better than the TPLF criminal? Are these not victims or Ethiopians? Are these victims not human beings? Certainly, the opposition media and their activists do not believe these victims are human or Ethiopians on their eyes. If they believe they are human and Ethiopians, why then is the opposition media and some claimed “activists” like Tamng Beyene do not want to talk about it?

How can I trust and march with these as real opposition and their media who do not want to bother for Human Rights or do not bother by tears flowing from the eye of the victims of Ginbot 7? Where is Ethiopia again heading? To a circle of another period of torture with these criminals controlling the political stage all over again? I need your answer.

Please spread it all over the Face book for the nation to hear such heart breaking tears. I cried for the victims when they broke into tears. Why not you? Explain to me why not you! Can any normal mind support these psychopathic criminals calling themselves Ginbot 7 who are giving our people to Eritreans to be tortured in the hand of Eritreans? Explain to me why you can’t stand against these human crime.

I will not buy any opposition propaganda when they talk freedom, liberty, humanity, unity, democracy…..when they intentionally stumble on such crime and ignore it as if nothing happen. It is a double standard. I have my doubts for years that these are not opposition but criminals. If they are not criminals, they aiding and abiding criminals. I am asking the Diaspora opposition to come clean on this issue, and demand a public protest against Ginbot 7 for its crime as you are protesting the TPLF crime. There is no better human being when it comes to torture, Torture who ever and where ever is carried against Ethiopians must be challenged by all peace loving people no matter who did it and where it is carried. It can be in Eritrea or Sudan, or Saudi , any torture against our people must be furiously challenged. Political criminals must be stopped before they introduce another third round system of torture in Ethiopia.

It is too embarrassing to witness such crime at this century committed by Ginbot 7 leaders  without any rumors or apology to their victims.
  
Visit this website to hear the audio video interview of the young and handsome Ethiopian Shitaw Shiferaw. http://www.ginbot7d.org/
  My email is getachre@aol.com Thanks Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay)